19/02/2026
በሶርጋ ሀይቅ ላይ የሚገኘው የሶርጋ ኢኮ ሎጅ በአሁኑ ወቅት በ14 ሄክታር መሬት ላይ እየተገነባ ይገኛል። የፕሮጀክቱ ስራ በፍጥነት እየተከናወነ ሲሆን በቅርቡ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። ከነቀምቴ ከተማ በ6 ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ ብቻ የሚገኘው የሶርጋ ኢኮ ሎጅ አካባቢውን ከመጠበቅ ባሻገር በኮንስትራክሽን እና በተለያዩ አገልግሎቶች የሥራ እድል እንዲፈጥር ተደርጎ የተቀረፀ ነው። ፕሮጀክቱ የአካባቢውን ማኅበረሰብ በመጥቀም በክልሉ ዘላቂ ቱሪዝምን የሚያበረታታ ይሆናል።