23/06/2026
ለሁሉን አቀፍ እድገት የስታርታፖች ሚና
የስራ ፈጠራ (ስታርታፕ) ዘርፍ ለኢኮኖሚ እድገት የላቀ ሚና እየተጫወተ ነው። በቅርቡ ካሊፎርኒያ በሚገኘውና ባሴቴን በተባለ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ስታርትአፕ ውስጥ የተመዘገበው 1.5 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት ፍሰት የኩባንያውን የገበያ ዋጋ ወደ 13 ቢሊዮን ዶላር ከፍ አድርጎታል። ይህ ክስተት በዓለም አቀፍ ደረጃ በቴክኖሎጂው ዘርፍ በተለይም በኤ.አይ ላይ እየዋለ ያለውን ከፍተኛ ካፒታል በግልጽ ያሳያል።
በኢትዮጵያም ተመሳሳይ የቴክኖሎጂ ሽግግር እየታየ ነው። የሀገሪቱ ስታርትአፖች በተደረገላቸው የመንግስት ድጋፍ አቅማቸውን በማጎልበት በፋይናንስ፣ በግብርና፣ በጤና እና በትምህርት ዘርፎች አገልግሎቶችን በማሻሻል ውጤታማ እየሆኑ ነው። እነዚህ ወጣት ባለሙያዎች ለሀገሪቱ ዲጂታል ጉዞ ጉልህ ሚና የሚጫወቱ ሲሆን የሥራ ዕድል በመፍጠር ለኢኮኖሚው ከፍተኛ አበርክቶ ይኖራቸዋል።ለ ስታርታፖች የሚደረገው ድጋፍ እና እየጎለበተ የመጣው አቅማቸው ኢትዮጵያ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ የምታደርገውን የዲጂታል ጉዞ የሚያጠናክር ነው።