Qali Miftac

Qali Miftac Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Qali Miftac, Grocers, Addis Ababa.

29/12/2025

ልዩ ዜና

👉የአርሚ 11 እና አርሚ 13 አዛዦች የጄነራል ታደሰ ወረደን ስብሰባ ረግጠው ወጡ!
👉በጊዜያዊ አስተዳደሩና በፅንፈኛው ቡድን መካከል ያለው ልዩነት የመጨረሻ ደረጃ ላይ ደርሷል!

የህወሃት ጉዳይ በጣም የሚያስገርም እንዲሆን የሚያሳዝን ሆኗል። ጌታቸው ረዳን አንፈልግም ታደሰ ወረደ ካልሆነ የአለም መጨረሻ ይሆናል ሲሉ የነበሩ ፅንፈኛው የህወሃት የፖለቲካ እና የታጣቂ አመራሮች በጄነራሉ ላይ ተነስተውበታል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጀ/ል ታደሰ ወረደ በታህሳስ 19/2018 ዓ.ም ከህወሓት ታጣቂ ቡድን የምዕራብ ግንባር የአርሚ አዛዦች እና ሎጂስቲክስ አመራሮች ጋር በሽሬ ከተማ ስብሰባ አካሂዶ ነበር። ይህ ስብሰባ በዋናነት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጊዜያዊ አስተዳደሩና በጽንፈኛው ቡድን መካከል እየታዩ የሚገኙ ልዩነቶችን ለመድፈን ያሰበ ቢሆንም ልዩነቶች የበለጠ የሰፉበትና ከፍተኛ መካረር የተፈጠረበት መሆኑን ከታማኝ ምንጭ ማረጋገጥ ተችሏል።

በተለይም የአርሚ 13 አዛዥ ፀጋዬ ማርከስ እና የአርሚ 11 አአዛዥ ፍስሃ ኪዳኑ (ወርቅ አይኑ) ጀ/ል ታደሰ በስብሰባው ያቀረበውን ሃሳብ ባለመቀበል ስብሰባውን አቋረጠው የወጡ መሆናቸውን ማወቅ ተችሏል። እስካሁን ባለው መረጃ ምንም እንኳን ስብሰባውን ረግጠው የወጡት ሁለት የአርሚ አዛዦች ቢሆን ሌሎች ተጨማሪ ከፍተኛ የቡድኑ አመራሮች የፕሬዘዳንቱን ሃሳብ ያለመቀበል አዝማሚያ እየታየባቸውና በቀጣይ ቀናትም ልዩነቱ ተባብሶ እንደሚቀጥል ይስተዋላል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ እነዚህ የአርሚ አዛዦች በፕሬዘዳንቱ ላይ መፈንቅለ መንግስት ሊፈፅሙ ይችላሉ በሚል በመቀሌ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Qali Miftac posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category