Ameya City Prosperity Party Branch Office

Ameya City Prosperity Party Branch Office ራዕያችን በግልፀኝነት ታማኝና ፈጣን መረጃ ለህዝብ በማድረስ የሁለንተናዊ ብልፅግና ማረጋገጥ ነዉ።

"ለአደጋ ስጋት ምላሽ መስጠት የሚያስችል ተቋማዊ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት ይገባል" :- አቶ ፍቅሬ አማንነሃሴ 05/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) በክልሉ በራስ አቅም የምግብ ዋስ...
11/08/2026

"ለአደጋ ስጋት ምላሽ መስጠት የሚያስችል ተቋማዊ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት ይገባል" :- አቶ ፍቅሬ አማን

ነሃሴ 05/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) በክልሉ በራስ አቅም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ከተረጂነት ለመውጣት በየአከባቢው የሚከናወኑ ተግባራትን ማጠናከር ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል፡፡

በውይይቱ በየዞኖች ድጋፋዊ ክትትል የሚያደርጉ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡

የውይይት መድረኩን የመሩት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን፣ ለአደጋ ስጋት ምላሽ መስጠት የሚያስችል ተቋማዊ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት ይገባል ብለዋል፡፡

የድጋፋዊ ክትትል ቡድኑ ጉድለቶችን መሙላት በሚያስችል መልኩ መከወን እንደሚጠበቅበትም ገልጸዋል፡፡

የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ፣ የሰብዓዊ ድጋፍ በራስ አቅም የሚለው አስተሳሰብ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡

አመራሩ መሠረታዊ የሆኑ ጉዳዮችን በመለየት መስራት አለበት ያሉት አቶ ነጋ፣ በተለይ የምግብ ክምችት፣ የመጋዘን ዝግጅት እና የግብርና ሥራዎች ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

የውይይቱ ተሳታፊዎች በመድረኩ በሰጡት አስተያየት በክልሉ በቂ የምግብ ክምችት ሊኖር ይገባል ብለዋል፡፡

የሚከማቹ ምግቦች ደግሞ በተገቢው መንገድ በተዘጋጁ መጋዘኖች መቀመጥ እንዳለባቸው ገልጸው፣ ሁሉም ወረዳዎች ለዚሁ ተግባር የተዘጋጁ መጋዘኖች ሊኖሩ ይገባልም ብለዋል፡፡

ለቅፀበታዊ አደጋዎች የሚሆን የምግብ፣ የውሃ እና ሌሎች ቁሳቁሶች ከወዲሁ በበቂ ሁኔታ እንዲዘጋጁ በተቋማት በጀት መያዝ እንደሚገባም ነው የገለጹት፡፡

ሁሉም ዜጎች ለአደጋ ስጋት መከላከል አስተዋጽኦ ማበርከት አለባቸው ሲሉም ተናግረዋል፡፡

አመራሩ የአገልጋይነት መንፈስ በመላበስ በሁሉም መስክ የህዝብን ዘላቂ ጥቅም የሚያረጋግጡ ግቦችን በላቀ ትጋትና ቁርጠኝነት እንድፈጽም ፓርቲ የመሪነት ሚና መጫወት አለበት ፦አቶ ፍቅሬ አማንበደ...
11/08/2026

አመራሩ የአገልጋይነት መንፈስ በመላበስ በሁሉም መስክ የህዝብን ዘላቂ ጥቅም የሚያረጋግጡ ግቦችን በላቀ ትጋትና ቁርጠኝነት እንድፈጽም ፓርቲ የመሪነት ሚና መጫወት አለበት ፦አቶ ፍቅሬ አማን

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራ አመራር ኮሚቴ የ2018 በጀት ዓመት ግቦች አፈጻጸም፣ በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ቅድመ ዝግጅትና የተለያዩ ተግባራትን በመገምገም የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

የስራ አመራር ኮሚቴው በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት የተቀመጡ ግቦችን በውጤታማነት በመፈፀም በፓርቲ መሪነት የህዝብ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በተደረገው ብርቱ ጥረት አመርቂ ውጤት የተገኘበት ዓመት መሆኑን ገምግሟል።

በመድረኩ በክልሉ የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን በየደረጃው የሚገኝ አመራርና አባል በበጀት ዓመቱ የተቀመጡ ግቦች በተቀመጠላቸው ጊዜ ገደብ ጥራታቸውን እና ፍጥነታቸውን ጠብቀው እንዲፈጸሙ በኃላፊነት መርተው አበረታች ውጤት መገኘቱን አንስተው በ2019 በጀት ለላቀ ውጤት መትጋት እንደሚገባ አሳስበዋል።

የፓርቲ መደበኛና የንቅናቄ አጀንዳዎችን በውጤታማነት በመምራት የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የአመራሩ ቀዳሚ ተግባር መሆኑን በመገንዘብ የተጀመረው ጥረት አበረታች መሆኑን የገለጹት ኃላፊው በ2019 በጀት ዓመት በየደረጃው ያለው መዋቅር ከወትሮው በበለጠ እንዲተጋ ለማስቻል ከታችኛው መዋቅር በጥልቀት ተግባቦት ለመፍጠር አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

አመራሩ የሕዝብ አገልጋይነት መርህ በመከተል በላቀ ትጋትና ቁርጠኝነት የህዝብ እርካታ የሚያሳድጉ የሰላም፣ የልማት እና የመልካም አስተዳደር እንዲሁም የመንግስትን የአገልግሎት አሰጣጥን በላቀ ትጋት በውጤታማነት ለመፈጸም ፓርቲ የመሪነት ሚና መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል።

የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ​በፓርቲ መሪነት የሚፈጸሙ ታላላቅ የልማት ኢኒሼቲቦችን በማስፋት ጥራታቸውን እና ዘለቀታቸውን አስጠብቀው መምራት እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።

በመጨረሻም የስራ አመራር ኮሚቴው በየደረጃው ያለው አመራርና አባላት ሰፊውን ህዝብ በማስተባበርና በመምራት የህዝቡን ዘላቂ ጥቅምና የክልሉን ሁለንተናዊ ዕድገት የሚያፀና ኃላፊነት እንዲወጣ አሳስበው በቀጣይ ጊዜያት የቅ/ጽ/ቤት መደበኛ ተግባራትና ልዩ ልዩ የንቅናቄ አጀንዳዎች አፈጻጸም ግምገማ እና 2019 በጀት ዓመት ፈጻሚ ማዘጋጃ መድረክ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በስፋት እንዲካሄድ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

"ህንግጫ" በዓል የማንነትነታችን መገለጫ ከመሆኑም ባሻገር የከተማችን ገጽታ ከፍ የሚያደረግ በመሆኑ ከባለፈው ዓመት ልምድ ወስደን ድክመቶችን በማረም ሁሉንም ባሳተፍ መልኩ በድምቀት ለማክበር ...
11/08/2026

"ህንግጫ" በዓል የማንነትነታችን መገለጫ ከመሆኑም ባሻገር የከተማችን ገጽታ ከፍ የሚያደረግ በመሆኑ ከባለፈው ዓመት ልምድ ወስደን ድክመቶችን በማረም ሁሉንም ባሳተፍ መልኩ በድምቀት ለማክበር ባለድርሻ አካላት ከወዲሁ ዝግጅት ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ

ይህ ተገለጸው የኮንታ ብሄር ዘመን መለወጫ "ህንግጫ" በዓል አከባበር ዕቅድና አደረጃጀት ዙሪያ የአመያ ከተማ አስተዳደር አብይ ኮሚቴ ውይይት ባካሄዱበት ውቅት ነው።

በከተማው የዘንድሮውን የኮንታ ብሄር ዘመን መለወጫ "ህንግጫ" ከወትሮ በተሻለ ድምቀት ለማክበር ከወዲሁ ሁሉም መዘጋጀት እንደሚገባ ተጠይቋል።

የውይይት መድረኩን የመሩት የአመያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተመስገን ደጄኔ እንደገለጹት፦ "ህንግጫ" በዓል የማንነትነታችን መገለጫ ከመሆኑም ባሻገር የከተማችን ገጽታ ከፍ የሚያደረግ በመሆኑ ከባለፈው ዓመት ልምድ ወስደን ድክመቶችን በማረም ሁሉንም ባሳተፍ መልኩ በድምቀት ለማክበር ባለድርሻ አካላት ከወዲሁ ዝግጅት ማድረግ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

አክለውም ከንቲባው በዓሉ ከታች ቀበሌ ጀምሮ ሁሉንም ባሳተፈ መልኩ በድምቀት እየተከበረ የሚመጣ በመሆኑ ከወትሮ በተሻለ ሁኔታ መከበር እንዳለበትና በዓሉን ለማክበር ህዝቡ በጉጉት መውጣት እንዳለበትና ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ስራዎች ላይ ኮሚቴ ትኩረት አድረጎ መስራት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።

በዋናነት ከወዲው የከተማችን ጽዳት ውበት ላይ በዓሉን በሚመስል መልኩ የማዘጋጀትና የማጽዳት ስራዎች በትኩረት ልሰራ ይገባል ብለዋል ከንቲባው።

የመወያያ ስነድ ያቀረቡት፦ የአመያ ከተማ አስተዳደር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ አበራ የበዓሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን የገለፁት ስሆን የዘንድሮውን በዓል ለማክበር የሚያስችሉ ዝግጅቶችን የሚያስተባብሩና ኮሚቴዎች ከወዲሁ ሚናቸውን በትኩረት ሊወጡ እንደሚገባ አስረድተዋል።

በ2019 ዓ.ም አከባበር ላይ ከባለፈው ዓመት ልምድ ወስዶ፣ ድክመቶችን አርሞ፣ ሁሉንም ባሳተፈ መልኩ በድምቀት ለማክበር ባለድርሻ አካላት ከዝግጅቱ ጀምሮ ርብርብ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየትም በዓሉን ከማክበር ባለፈ የብሔረሰቡ ባህል፣ ታሪክ፣ ቋንቋና እሴቶች ተጠንተውና ተደራጅተው ለትውልድ እንዲተላለፉ ተኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት አንስተው እነሱም የድርሻቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።

ዘገባው፦ የአመያ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

በ2018 ትምህርት ዘመን የታዩ ጉድለቶችን በማረም የጥራትና የተደራሽነት ማነቆዎችን በመቅረፍ የ2019 ትምህርት ዘመንን በተሻለ ቁመና መምራት ያስፈልጋል - ከንቲባ ተመስገን ደጄኔበኮንታ ዞን...
10/08/2026

በ2018 ትምህርት ዘመን የታዩ ጉድለቶችን በማረም የጥራትና የተደራሽነት ማነቆዎችን በመቅረፍ የ2019 ትምህርት ዘመንን በተሻለ ቁመና መምራት ያስፈልጋል - ከንቲባ ተመስገን ደጄኔ

በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳደር የማህበራዊ ክላስተር ትምህርት ዩኒት ''የጋራ ትጋት ለትምህርት ልማት እመርታ'' በሚል መርህ ቃል የተዘጋጀ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ልማት ሥራዎች አፈጻጸም ግምገማና የ2019 ዓ.ም የከተማ አቀፍ የትምህርት ንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩ የአመያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተመስገን ደጄኔ እንዳሉ፦ ትምህርት ለእድገት ሁሉ መሠረት እንደመሆኑ መጠን የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እና የሚፈለገው ውጤት ለማምጣት ባለድርሻ አካላትና ማህበረሰብ ተቀናጅቶ መሰራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

የትምህርት ሥራዎችን እያንዳንዱን እንቅስቃሴ በቅርበት ባለመከታተል የተመዘገበው ዝቅተኛ ውጤት በ2019 ዓ.ም ለማካካስ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሀላፊነት መውሰድ እንዳለባቸው ያሳሰቡት ከንቲባው ለውድቀቱ ምክንያት ከመስጠትና ውድቀትን ወደ ሌሎች ከማንከባለል ይልቅ «ችግሩን የፈጠርኩት እኔው ነኝ» በሚል ሀላፊነት በመውሰድ ለቀጣይ የተሻለ ውጤት በትጋት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

አያይዘውም ከንቲባ፦ የመማሪያ ማስተማር ሥራዎችን ከወትሮ በበለጠ ለማቀላጠፍ በዋናነት የትምህርት ባለድርሻ አካላት ትኩረት ተሰጥተው መሰራት እንዳለበት አሳስቧል።

የአመያ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ወንድሙ ዋጌ እንደገለጹ፦ ትውልድ ለመቅረፅና ሀገር ለመገንባት የሚያስችል መሠረት እና ቁልፍ ጉዳይ ትምህርት በመሆኑ በዘርፉ የገጠመውን ስብራት በመጠገንና በማከም የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ለማጠናከር ትምህርት ላይ ልዩ ቁርጠኝነት ተሰጥቶ መሰራት እንደሚያስፈልግ ተናግሯል።

አክለው፦ በትምህርት ዘርፍ ያልተሰራበት ውጤት መጠበቅ ከባድ መሆኑን ጠቁመው፣ በትምህርት ስራ ላይ የመጣው ዝቅተኛ ውጤት የሥራ ክፍተቶችን የሚያሳይ በመሆኑ በትምህርት ላይ ያለውን አቋም በመቀየር በጋራና በአንድነት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የከተማ አስተዳደር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ አበራ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ስራ አፈፃፀምና የ2019 ዓ.ም ዕቅዱን ያካተተ ስነድ ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩ፦ በትምህርት ዘርፍ በከተማው የተሻለ ትውልድን ለመፈጠር ሁሉም ባለድርሻ አካላት ያለ ስስት የሚጠበቅባቸውን ድርሻ መወጣት እንዳለባቸው ጠቁሟል።

በ2019 የትምህርት ዘመን የሚማሩ ተማሪዎች ምዝገባን በጊዜ ለማጠናቀቅ በሁሉም ትምህርት ቤቶች አስፈላጊ ዝግጅት መደረግ እንዳለባቸው አሳስቧል።

የተማሪ ቅበላን ጨምሮ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል በተደራጀ መልኩ የማጠናከሪያ ትምህርት መስጠት፣ ማህበረሰቡን በገንዘብ፣ በጉልበት፣ በእውቀትና በዓይነት ድጋፍ ማሳተፍ እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ መምህራን ምደባና ድልድል በልዩ ትኩረትና በፍትሃዊነት መፈጸም የዕቅዱ አካል ተደረገው መሰራት እንዳለበት ጠቁመዋል።

በመጨረሻም የመድረኩ ተሳታፊዎች የታዩ ጉድለቶችን በጥልቀት በመገምገም እና የህዝብ ንቅናቄ በመፍጠር የትምህርት ዘርፉን ወደተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

ዘገባው፦ የአመያ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

የጋራ ትጋት ለትምህርት ልማት እመርታ "በሚል መሪ ቃል የትምህርት ንቅናቄ መድረክ በአመያ ከተማ አስተዳደር እየተካሄደ ነው በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳደር የማህበራዊ ክላስተር ትምህርት ...
10/08/2026

የጋራ ትጋት ለትምህርት ልማት እመርታ "በሚል መሪ ቃል የትምህርት ንቅናቄ መድረክ በአመያ ከተማ አስተዳደር እየተካሄደ ነው

በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳደር የማህበራዊ ክላስተር ትምህርት ዩኒት ''የጋራ ትጋት ለትምህርት ልማት እመርታ'' በሚል መርህ ቃል የተዘጋጀ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ልማት ሥራዎች አፈጻጸም ግምገማና የ2019 ዓ.ም የከተማ አቀፍ የትምህርት ንቅናቄ መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በንቅናቄ መድረኩ በ2018 ዓ/ም በዘርፉ የተከናወኑ ዋና ዋና የትምህርት ልማት ሥራዎች አፈጻጸምና ቀጣይ የንቅናቄ ስራዎችን የያዘ ሰነድ ቀርበው ውይይት ይደረጋል።

በንቅናቄ መድረክም የከተማ አስተዳደር አስተባባሪ አካላት፣ የከተማው ፑል አመራሮች፣ የዞን ትምህርት መምሪያ ከፍተኛ ባለሙያዎች፣ የቀበሌ አመራሮች፣ ርዕሰ መምህራንና ሱፐረቫይዘሮችን ጨምሮ አጠቃላይ የትምህርት ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

ዘገባው፦ የአመያ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

በከተማው በአንድ ጀምበር 2 ሚልዮን 500 የመኖ ችግኝ ተከላ ይፋዊ ማስጀመሪያ መርኃግብር ተካሄደ በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳደር በአንድ ጀምበር 2 ሚልዮን 500 የመኖ ችግኝ ተከላ ይፋ...
10/08/2026

በከተማው በአንድ ጀምበር 2 ሚልዮን 500 የመኖ ችግኝ ተከላ ይፋዊ ማስጀመሪያ መርኃግብር ተካሄደ

በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳደር በአንድ ጀምበር 2 ሚልዮን 500 የመኖ ችግኝ ተከላ ይፋዊ ማስጀመሪያ መርኃግብር በአመያ 03 ቀበሌ ተካሂዷል።

በማስጀመሪያ መርሀ-ግብሩ ላይ የተገኙት የአመያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተመስገን ደጄኔ እንደገለፁት፦ የእንስሳት መኖ ችግኝ ተከላው የሌማት ትሩፋት ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል።

የእንስሳትን ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር የእንስሳትን መኖን በመትከልና ዝርያን ማሻሸል ዋናው ተግባር መሆኑን የገለፁት ከንቲባው የእንስሳት መኖ ሳር ተከላ ስራን በማስፋፋት የመኖ ልማትን በማዘመን የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።

የአካባቢውን የእንሰሳት ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እንዲሁም የወተትና ሥጋ አቅርቦትን ለማሻሻል መሰል የተከላ መርሃግብሮች ቀጣይነት ሊኖራቸው እንደሚገባ ተመላክቷል።

የአመያ ከተማ አስተዳደር ኢንተርፕራይዝ፣ ከተማ ግብርና፣ ህብረት ስራ፣ መንገድ ትራንስፖርት ክላስተር አስተባባሪ አቶ ወንድማገኝ ወዳጄ በበኩላቸ፦ በከተማው በአንድ ጀምበር እየተካሄደ ባለው የመኖ ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሃግብር በአንድ ጀምበር 45.5 ሄክታር መሬት ላይ 2 ሚልዮን 500 የመኖ ችግኞች ለመትከል መታቀዱን ገልጸዋል።

በተለይ በከተማው የወተት መንደሮች ላይ የመኖ ተከላ ስራዎች ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ሲሆን ከአረንጓዴ ልማት ዘርፍ አንዱ የሆነውን የመኖ ተከላ አጠናክሮ ማስቀጠል ወሳኝ ሲሆን ዛሬ የተተከለው መኖ ነገ ወተት እና ስጋ ሆኖ ምግብ ከመሆን ባሻገር የገቢ ምንጭ ሆኖ ያገለግላል ብለዋል።

በአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ መርሀ ግብሩም የከተማ አስተዳደር አስተባባሪ አካላ፣ የዞኑ ግ/አ/ህ/መምሪያ አመራሮችና ከፍተኛ ባለሙያዎች፣ የከተማው አጠቃላይ አመራሮች፣ መንግስት ሰራተኞች፣ ወጣቶችን ጨምሮ ሌሎች ህብረተሰብ ክፍሎች በነቂስ ወጥቶ ተሳትፏል።

ዘገባው፦ የአመያ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

የኮንታ ልማት ማህበር ስራ አመራር ቦርድ መደበኛ ስብሰባዉን አካሄደ።የማህበሩ ሥራ አመራር ቦርድ በ2026 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸምና ሌሎች አጀንዳዎች ላይ ዝርዝር ዉይይት አካሂ...
10/08/2026

የኮንታ ልማት ማህበር ስራ አመራር ቦርድ መደበኛ ስብሰባዉን አካሄደ።

የማህበሩ ሥራ አመራር ቦርድ በ2026 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸምና ሌሎች አጀንዳዎች ላይ ዝርዝር ዉይይት አካሂዷል።

የቦርዱ አባላትም በልማት ማህበሩ ስር የሚተዳደሩ የተለያዩ ፕሮጀክቶችና ተቋማትን ጉብኝት አድርገዋል።
‎‎
‎የልማት ማህበሩ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ነጋ አበራ የኮንታ ልማት ማህበር የህዝብ ተቋም በመሆኑ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሥራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ሀብት በማመንጨት እና ከህብረተሰቡ ለሚነሱ ጥያቄዎች አቅምን ማዕከል ያደረገ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ አበረታች ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው ማህበሩ አደረጃጀቱንና አሰራሩን አዘምኖ በተሻለ ቁመና ላይ እንዲገኝ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ሊመሩ እንደሚገባ ገልፀዋል።

‎በእስካሁኑ አፈፃፀም የታዩ ውጤቶችን ለማስቀጠልና ጉድለቶችን ለመቅረፍ የተጀመረዉን ተቋማዊ ሪፎርሙን በማሳለጥ በበለጠ ትጋት መስራት እንደሚያሻም አስረድተዋል።

ልማት ማህበሩ በስሩ የሚገኙ የኢሞታ ልዩ አዳሪ ት/ቤትን ጨምሮ ሌሎች የገቢ ማስገኛና አገልግሎት ሰጪ ፕሮጅክቶችን ከአደረጃጀትና አሰራር አንፃር ዘመናዊና ነፃነቱን በጠበቀ መልኩ መመራት እንዲችሉ አጋዥ አሰራሮች ላይም በዝርዝር ዉይይት አድርጎ ዉሳኔ አስተላልፏል።

በቀጣይም የኮንታ ልማት ማህበር ህዝባዊ መሠረት እንዲይዝ መስራት፣ አዳዲስ አባላትን ማፍራት፣ በገቢ አሰባሰብ ላይ ትኩረት መስጠት፣ ማህበረሰባዊ ስራዎችን አጠናክሮ መምራት ላይ በትኩረት እንዲሰራ አቅጣጫ ተቀምጦ መደበኛ ስብሰባው ተጠናቋል።
ዘገባው የኮንታ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው

ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ይበልጥ ቀልጣፋ ማድረግ፣ የተቋሙን የውስጥ አቅም ማሳደግ እና የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትን ይበልጥ የማስፋፋት ስራ ለተቋሙ የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫ ልሆን ...
08/08/2026

ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ይበልጥ ቀልጣፋ ማድረግ፣ የተቋሙን የውስጥ አቅም ማሳደግ እና የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትን ይበልጥ የማስፋፋት ስራ ለተቋሙ የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫ ልሆን ይገባል - የቦርዱ ስብሳቢ አቶ ተመስገን ደጄኔ

የኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳደር ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የቦርዱ አባላት የ2018 በጀት ዓመት የአፈፃፀም ግምገማና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ ዝግጅት ዙሪያ የግምገማ ነክ ውይይት መድረክ አካሂዷል።

ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት በ2009 ዓ.ም በከተሞቹ ጥናት በማድረግ በራሳቸው ቦርድ ሥራ አመራር እየተመሩ ለህብረተሰቡ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት በመስጠት በከመንግስት ጥገኝነት መላቀቅ ይታወሳል።

በመድረኩ የአመያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባና የቦርዱ ስብሳቢ አቶ ተመስገን ደጄኔ እንደገለፁት፦ የከተማ ውሃ አገ/ሎት ድርጅት በበጀት ዓመቱ ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ፣ ጥራት ያለውና ተደራሽ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት በርካታ አበረታች ስራዎች ማከናወኑን ጠቅሷል።

የከተማ ውሃ አገ/ሎት ድርጅት አላማው የድርጅቱ ውስጥ ገቢ ማሳደግ የከተማ ውሃ ብክነት መቆጣጠር የደንበኛ ጥያቄና ፍላጎት መሠረት በማድረግ የንፁህ መጠጥ ዉሃ ችግር ያለባቸውን አከባቢ በመለየት ዙሪያ የተሰሩ ስራዎች አበረታች ቢሆንም በቀጣይም ለስራው ስኬት ሁላችንም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል ከንቲባው።

የዞኑ ውሃ ማዕድን ኢነርጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ ጣላርጎ መኮንን በበኩላቸው፦ መንገድ፣ውሃና መብራት ለከተማው ማህበረሰብ መሠረታዊ ነገሮች በመሆናቸው በከተማ አስተዳደር መዋቅር ከመቼውም ጊዜ በላይ በትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባ የገለፁት ሲሆን ሁሉምን መንደር ውሃ የማድረስ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግሯል።

በውሃ አገልግሎት ድርጅቶች የሚስተዋሉ ከፍተቶችን በማረም ለተገልጋዩ ህ/ሰብ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት በተቋሙ የሰለጠነ የሰው ኃይል በማደራጀት የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍና እንዲሻሻል የቦርድ ሥራ አመራር ሚና የላቀ መሆኑም ገልጿል።

በከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ሰራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ቡልቻ የ2018 በጀት ዓመት የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት ባቀረቡት ወቅት እእንደተናገሩት፦ አዳድስ የውሃ ተቋማት ግንባታና የነባር የውሃ ተቋማት ማስፋፊያ እንዲሁም ነባር ተቋም ብልሽት ደረጃ በመለየትና በመጠገን ህብረተሰቡ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ እንዲሆን ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ መቆየቱን ገልጸዋል።

አያይዘውም አቶ ዮሴፍ እንዳሉት፦ የቦርድ ሥራ አመራር በሚያስቀምጡ አቅጣጫ መሠረት የታዩ ጉድለቶችን በማረም በተቋማቱ ጠንካራ ቅንጅታዊ አሰራርን በመዘርጋትና በማጠናከር ለቀጣይ ስራ እንቅስቃሴ ችግሮችን በመለየት በልዩ ቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በከተማ ውሃ አገልግሎት ደረጃ የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ማነቆዎችን ለማስቀረት ችግሮችን በማረምና በመቆጣጠር ለህብረተሰቡ በቂ የውሃ አገልግሎት ለማቅረብ በትኩረት ሊሰራ ይገባልም ብሏል።

ዘገባው፦ የአመያ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

''ህንግጫ'' በርካታ ባህላዊ እና ማህበራዊ እሴቶችን የያዘ የማንነት መገለጫ በዓል ነው።  የመድረኩ ተሳታፊዎች በኮንታ ዞን የኮንታ ብሔር ዘመን መለወጫ "ህንግጫ" ክብረ በዓል የጥናት ሰነድ...
07/08/2026

''ህንግጫ'' በርካታ ባህላዊ እና ማህበራዊ እሴቶችን የያዘ የማንነት መገለጫ በዓል ነው። የመድረኩ ተሳታፊዎች

በኮንታ ዞን የኮንታ ብሔር ዘመን መለወጫ "ህንግጫ" ክብረ በዓል የጥናት ሰነድ ግምገማ እና የቫሊዴሽን መድረክ ተካሂዷል።

በኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በኩል
የ''ህንግጫ'' በዓል ታሪካዊ ዳራ፣ የበዓሉ መዳረሻና ባህላዊ እሴቶች ላይ ያጠነጠነ ጥናታዊ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

የውይይት መድረኩን የመሩት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ የ''ህንግጫ'' በዓል በርካታ ባህላዊ እና ማህበራዊ እሴቶችን የያዘ የማንነት መገለጫ በዓል መሆኑን ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ የብዝሃ ታሪክ፣ ባህል፣ ቋንቋና ብዝሃ ማንነቶች ከሚንጸባረቅባቸው ጥቂት የዓለም ሀገራት አንዷ መሆኗን የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው ኮንታም የዚህ ፀጋ ተቋዳሽ በመሆኗ የህንግጫ በዓል አንዱ ማሳያ መሆኑን አመልክተዋል።

በዚህም የኮንታ ብሔር የዘመን አቆጣጠር ከኢትዮጵያ ካላንደር አቆጣጠር ሳይጣረስ የራሱ የሆነ አቆጣጠርና ስያሜ ያለው ሲሆን ዓመታትን፣ ወራትንና ሳምንታትን የሚቆጥርበት ስርዓት ያለው ብሔር መሆኑን አመላክተዋል።

የኮንታ ብሔር ዘመን መለወጫ የ"ህንግጫ" በዓል ተጠንቶ፣ ተሰንዶ እና ከነሙሉ ክብሩ መልካም እሴቶችን አስጠብቆ ለትውልድ ማሸጋገር እንዲቻል ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበው በቀጣይ ተግባራት ላይ ሁሉም የብሔሩ ተወላጆችና ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

የዞኑ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አበበ ደምሴ በበኩላቸው የህንግጫ በዓልን ለማልማት፣ ለማስተዋወቅና ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማሸጋገር ሰፊ ስራዎች ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመዋል።

የበዓሉን ታሪካዊና ባህላዊ እሴቶችን በዘላቂነት ለማስጠበቅና ለማስተዋወቅ በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር ማስደገፍ ወሳኝ መሆኑን የጠቆሙት ኃላፊው በክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ አስተባባሪነት፣ በዞን አስተዳደር ድጋፍና በፌዴራል ባህልና ስፖርት ሚኒስተር አማካይነት የብሔረሰቡ ዘመን መለወጫ ህንግጫ በዓል ጥናት ስራ መካሄዱን ገልፀዋል።

የጥናቱ ዋና ዓላማ የበዓሉን መነሻ ታሪክ፣ ማህበራዊ እሴቶች፣ ባህላዊ ስርዓቶችና ትርጉሞችን በሳይንሳዊ መንገድ በማስጠናት ለባህል ጥበቃ ለቱሪዝም ልማትና ወደፊት በዓለም-አቀፍ በማይደሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ መሠረት የሚጥል ጠቃሚ ጥናት ነው ብለዋል።

የጥናቱ ሰነድ በኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሙያ በሆኑት በአቶ ማህተቤ ጥላሁን አማካኝነት የቀረበ ሲሆን ከሰነዱ መነሻ ሀሳብ አስተያየት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።

ዘገባው የኮንታ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ህዩዋ...ባላ ህዩዋ…. እንኳን አደረሳችሁ፡፡ ጳጉሜ 1 በታላቅ ድምቀት የሚከበረው "ህንግጫ" የልምላሜው መልክ፤ የኮንታ ብሔረሰብ አዲስ ዓመት፤የኮንታ ብሔረሰብ በርካታ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ...
06/08/2026

ህዩዋ...ባላ ህዩዋ…. እንኳን አደረሳችሁ፡፡

ጳጉሜ 1 በታላቅ ድምቀት የሚከበረው "ህንግጫ" የልምላሜው መልክ፤ የኮንታ ብሔረሰብ አዲስ ዓመት፤

የኮንታ ብሔረሰብ በርካታ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ባህላዊ፣ ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ ቅርሶችና ዕሴቶች ባለቤት መሆኑ እሙን ነው፤ ከእነዚህ ውብ ዕሴቶች አንዱ የሆነው የብሔረሰቡ የዘመን መለወጫ/ህንግጫ/ በዓል አንዱ ነው።

የኮንታ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ /ህንግጫ/ በዓል በብሔረሰቡ ዘንድ በየዓመቱ በታላቅ ጉጉት ተጠብቆ የሚከበር ልዩ በዓል ሲሆን ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲሻገር ባህላዊ ይዘቱን ጠብቆ ነው፡፡ እሴቱ ሳይጎድልና ውበቱ ሳይደበዝዝ እዚህ የደረሰ የብሔረሰቡ የማንነት መገለጫም ነው፡፡

ህንግጫ በኮንታ ብሔረሰብ አጠራር ያማረ፣ ያጌጠ፣ የለመለመ ማለት ሲሆን አደይ አበቦች ፈክተው የሚታዩበት፣ የክረምቱ ወራት አልፎ የጠራ ሰማይ የሚታይበት፣ አርሶ አደሮች የክረምት አዝመራቸውን አገባደው ከአረምና ኩትኳቶ ስራ አርፈው ለመልካም ፍሬ ተስፋ የሚሰንቁበት ወቅት በመሆኑ በብሄረሰቡ ዘንድ በልዩ ትኩረትና በተስፋ የሚከበር ልዩ በዓል ነው።

የህንግጫ በዓል ሲከበር ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲሱ ዓመት መሸጋገሪያ እንደመሆኑ በዕለቱ ሁሉም ጠግበው፣ ጎዶሎው ሞልቶ፣ ያለው ለሌለው አካፍሎ የሚበላበት፣ ድሃ ከሀብታም እኩል የሚያከብሩት፣ መጥፎ ነገር ሁሉ ቀርቶ መልካም መልካሙ እንዲሸጋገር ፈጣሪውን የሚለምንበት የጥጋብና ሙሉ የመሆን አስተምህሮ የሚገለፅበት የተስፋ በዓል ነው።

እንደ ባህሉ ትውፊት ህንግጫ ከጳጉሜ የመጨረሻዋ ቀን እስከ መስከረም 30 ድረስ ደምቆ ይከበራል። ከቤት እስከ ደጃፍ አካባቢ ይፀዳል፤ ከአሮጌው ዓመት የሚሻገር እድፍና ጉድፍ እንዳይኖር ይጠረጋል፤ ምድር ትዋባለች፡፡

ህንግጫ ከ12 ዓይነት በላይ የሆነው የኮንታ ባህላዊ ምግብ ተዘጋጅቶ የሚቀርብበት የባህል አውድም ነው፡፡ የዘመን መለወጫ በዓል ማብሰሪያ እሳት የሚወጣው ጳጉሜ የመጨረሻዋ ቀን ነው፡፡

በህንግጫ ወቅት ‹‹ሙጬ ›› ማለት ከጳጉሜ 1 እስከ ጳጉሜ 5/6 ድረስ ያሉ ቀናትን የሚያመላክት ሲሆን በእነዚህ ቀናት ዉስጥ እህል በተለይም ጤፍ ቢዘራ የማይበቅልና ቢበቅልም እንኳን ከግንዱ ተቆርጦ የሚወድቅና እንዲሁም ሳያድግ ቀጭጮ ስለሚቀር ወቅቱ ‹‹ ሙጬ ›› ተብሏል፡፡

በመሆኑም ‹‹ ሕንግጫ ›› የሚለዉ የብሔሩ የዘመን መለወጫ በዓል እንደሆነ የዕድሜ ባለፀጋዎችና የተለያዩ የታሪክ መጽሐፍቶች ይመሰክራሉ፡፡

የኮንታ ህዝብ የዘመን መለወጫ በዓል ማክበር የጀመረዉ በኦሞ፣ በጎጀብ እና በዝግና ተፋሰስ መኖር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በዓሉን ሲያከብሩ እንደ ነበረ ይነገራል፡፡

ሆኖም በዓሉ መቼና እንዴት ተጀምሮ እያደገ እንደመጣ ትክክለኛውን ጊዜ የሚጠቁም የጽሑፍ መረጃ ባይኖርም ለበዓሉ ታሪካዊ አመጣጥ የራሱ አመልካች መረጃዎች እንዳሉ ቀደምት አባቶች በአፈ-ታሪክ ያረጋግጣሉ፡፡

ይህም በኮንታ መንግሥት ተመስርቶ ግዛቱን ተቆጣጥሮ መኖር ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ማለትም የመጀመሪያው የአራ የዘር ግንድ ቀዳሚ ንጉስ “ከካቲ ኤማዶ” ዘመነ መንግስት በ12ኛዉ መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ ይበልጥ በተጠናከረ ሁኔታ በቤተሰብ ደረጃም ሆነ ከጎረቤት ጋር በጋራ በመሆን በዓሉን እያከበሩ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ መሆኑ በታሪክ ይነገራል፡፡

‹‹ህንግጫ›› ማለት እንደ ብሔሩ አባቶችና የታሪክ ምሁራን አገላለጽ የሁለት ቃላት የ‹‹ሂን›› እና የ‹‹ጊጫ›› ዉህድ ሲሆን ‹‹ሂን›› ማለት ወደዚያ አስፋ/ፊ ሲሆን ‹‹ጊጫ›› ማለት አሳምር፣ ጥረግ፣ አጽዳ፣ ፋቅ (Giid’ara) የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡

በመሆኑም ከዕለቱ በዓል ጋር የሚያ

Address

Ameya
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ameya City Prosperity Party Branch Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category