Dawit wate werera

Dawit wate werera Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dawit wate werera, Grocers, Bule, Dila.

24/08/2026

የዘመን አቆጣጠር ተሻሻለ‼ ከዓ.ም👉ኢ.አ

የሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ዋና ዋና ውሳኔዎችና ያልተቋጩ አጀንዳዎች

​ለ38 ቀናት ሲካሄድ የቆየውና 400 ምክረ-ሀሳቦች የቀረቡበት ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ መጠናቀቁ ተገለጸ። ከተስማሙባቸውና በልዩነት ከተያዙት መካከል ዋና ዋናዎቹ፦

​✅ ስምምነት የተደረገባቸው፦

📌​የዘመን አቆጣጠር፦ «ዓመተ ምህረት (ዓ.ም)» የሚለው ቀርቶ «የኢትዮጵያ አቆጣጠር (ኢ.አ)» እንዲባል፤ «ሒጅራም» እንደ ካላንደር እንዲካተት።

📌​አንቀጽ 39፦ «እስከ መገንጠል» የሚለው ድንጋጌ እንዲሰረዝ።

📌​የስራ ቋንቋ፦ አማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ፣ ትግርኛ፣ ሶማሊኛ እና አፋርኛ የፌዴራል የስራ ቋንቋዎች እንዲሆኑ (ብሔራዊ ቋንቋ ግን ለጊዜው አያስፈልግም ተብሏል)።

📌​ውህድ ማንነት፦ ከሁለት በላይ ብሔሮች የተወለዱ ዜጎች «በውህድ ማንነት» እውቅና እንዲሰጣቸው።
​የመንግስት አወቃቀር፦ «ፌዴራላዊ» ሆኖ እንዲቀጥል።

​❓ በልዩነት የተያዙ (ያልተወሰኑ) 4 ነጥቦች፦

📌​የአዲስ አበባ ጉዳይ፦ የፌዴራል ተጠሪነቷና የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ ከተማነት/መብት ሁኔታ - አሁን ባለበት ነው።

📌​የመንግስት ቅርጽ፦ «ፓርላሜንታዊ» ወይስ «ፕሬዚዳንታዊ» ይሁን የሚለው።

📌​ሰንደቅ ዓላማ፦ አሁን ያለው አርማ ይ ቀጥል ወይስ በሌላ ይተካ።

📌​የፌዴሬሽን ምክር ቤት፦ አባላቱ በህዝብ በቀጥታ ይመረጡ ወይስ በክልሎች።

​📌 ኮሚሽኑ በልዩነት የተያዙትን አደራጅቶ ውሳኔ ለሚሰጠው አካል እንደሚያቀርብ አስታውቋል።(ቲክቫህኢትዮጵያ)
Wasu Mohammed - Mereja

22/08/2026
13/08/2026
09/08/2026

ኢትዮጵያ ሰላም ያስፈልጋታል፤ ተጨማሪ ጦርነት አይደለም!" — ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ለአመራሮችና ለመላው ኢትዮጵያውያን ያስተላለፉት ጥብቅ የሰላም ጥሪ

የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ዋና ዳይሬክተር ኢትዮጵያዊዉ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በሀገራችን ኢትዮጵያ በየአቅጣጫው እየተስፋፋ ባለው ግጭት፣ የሰው ሕይወት ማጣት እና የንብረት ውድመት ላይ ያላቸውን ጥልቅ ሀዘን በመግለፅ፣ በአስቸኳይ ጦርነቶች ቆመው ወደ ሰላማዊ ውይይት እንዲገባ ጥሪ አቀረቡ።

ዶ/ር ቴዎድሮስ ባስተላለፉት መልእክት በኢትዮጵያ ልዩ ልዩ ክልሎች እየተካሄዱ ያሉ ግጭቶች በህዝቡ ህይወትና በሀገሪቱ የወደፊት እድል ላይ እያደረሱ ያሉትን ከባድ ጉዳት በዝርዝር አስቀምጠዋል፦

1. በአማራ ክልል፦ ላለፉት ሦስት ዓመታት ሲካሄድ የቆየው የታጠቀ ግጭት የበርካታ ንጹሃን ዜጎችን ሕይወት ቀጥፏል፤ የማህበረሰቡን ሰላምና ኢኮኖሚም አቃውሷል።

2. በኦሮሚያ ክልል፦ አሁንም ድረስ የቀጠለው ግጭት እና ደም መፋሰስ በዜጎች ላይ ያልተቋረጠ ሰቆቃና ስቃይ እያስከተለ ይገኛል።

3. በትግራይ ክልል፦ ክልሉ እንደገና ወደ ክፍትና አደገኛ ጦርነት የመንሸራተት ከባድ ሥጋት ደቅኗል።

4. በአፋር ክልል፦ የአካባቢው ማህበረሰብ ካልፈለገበትና ካልተገባበት ግጭት ውስጥ እየተሳበ ይገኛል።

5. በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፦ አካባቢው አሁንም ቢሆን በሁከት፣ በ አለመረጋጋት እና በኃይል ድርጊቶች መዳፍ ውስጥ ወድቆ ይገኛል።

ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የፌዴራል መንግሥት፣
የክልል አመራሮች እና ሁሉም ባለድርሻ አካላት ከመሣሪያ እና ከኃይል አማራጭ ይልቅ የሰላምና የውይይት መንገድን እንዲመርጡ በአጽንኦት ጠይቀዋል።

በተጨማሪም ጦርነት መቼም ቢሆን ዘላቂ መፍትሔ አምጥቶ እንደማያውቅና የሚያስከትላቸው የከፉ ውጤቶች አራት ዋና ዋና ነገሮች መሆናቸውን አብራርተዋል፦

* የሰው ሕይወት ማጣትና ሞት
* የሀገር እና የማህበረሰብ ሀብት ውድመት
* የዜጎች መፈናቀልና ቤት አልባነት
* ከባድ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መከራ (ሰቆቃ)

"ኢትዮጵያውያን ከዚህ የተሻለ የሰላም፣ የዕድገት እና የአንድነት ሕይወት ይገባቸዋል። የፖለቲካ ልዩነቶች መፈታት ያለባቸው በጠመንጃ ሳይሆን በእውነተኛና በቅንነት በተሞላ የፖለቲካ ውይይት ብቻ ነው።

ይህ መልእክት በየደረጃው ላሉ አመራሮች ብቻ ሳይሆን፣ ሰላምን ለሚመኙ መላው የኢትዮጵያ ሕዝቦች የቀረበ የህሊና ጥሪ ነው።

Via የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ዋና ዳይሬክተር ኢትዮጵያዊዉ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም

ጉርሻ page

🌴🌴🌴

05/08/2026

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ ቀን ላይ የታየው በጎነት
==========*************===========

ዲ.ዩ: ሐምሌ 29/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)

በጎ ስራን መከወን የአዕምሮ እርካታን ይሰጣል። መንፈስን ያድሳል። ብዙዎች በጎ ተግባርን ስራቸው አድርገው ከቃል በላይ በተግባር ይኖሩታል፣ ለበርካቶች የደስታ ምንጭ ሆነው በደጋጎች መንደር የማይፋቅ ስማቸውን ይጽፋሉ።

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከመማር ማስተማር ስራቸው በተጓዳኝ፣ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች ላይ በንቃት እንዲሳተፉ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት፣ ዘርፉ ብዙ የበጎ አድራጎት ተግባራትን ያከናውናሉ። ዲላ ዩኒቨርሲቲም በዚሁ መነሻነት ከሰሞኑ የክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራን አስጀምሯል። በማስጀመሪያ መድረኩ ላይም እጅግ የሚያስደስት ተግባርን ፈጽሟል።

አብዛኛው የዲላ ከተማ ነዋሪ ያውቀዋል። የሰባት ዓመት ታዳጊ ሲሆን፣ በዚህ እድሜው አካል ጉዳተኛ ሆኖ እንደ ሌሎች ጓደኞቹ መማር ሲገባው ከትምህርት ማዕድ ርቆ የዕለት ጉርሱን ፍለጋ ሲንከራተት ለሚያይ ሁሉ እጅጉን ይከብዳል።

ታዳጊው ህፃን ተመስገን አየለ ይባላል። ያለ ወላጅ እናት ከወላጅ አባቱ ጋር በዲላ ከተማ የጎላ ቀበለ ነዋሪ ነው። ምንም ዓይነት የውጭ ድጋፍ እና እገዛ እንደሌለው የሚናገረው ይህ ታዳጊ ህፃን፣ ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ህይወት የሰጠችሁ ከባዱ ፈተና እንደሆነ ይገልፃል።

በተለይ ደግሞ ቀን በጠራራ ፀሐይ ከቦታ ቦታ የሚንቀሳቀሰው ያለምንም መርጃ መሳሪያ መሆኑ፣ ፈተናውን እጅግ ከባድ ያደርገዋል። ገና በዚህ ዕድሜው ከፈተናዎች ጋር እየተጋፈጠ የሚታትርን ታዳጊ ህፃን ታዲያ ዲላ ዩኒቨርሲቲ የጤናው ዘርፍ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ ወቅት ላይ የዊልቸር ድጋፍ አበርክቶለታል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር)በወቅቱ እንደተናገሩት፣ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራን በእንዲህ ባለ መንፈስን በሚያድስ ተግባር መጀመር እጅጉን እንደሚያስደስት ገልፀው፣ የተደረገው የዊልቸር ድጋፍም ታዳጊው ያለበትን ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ ችግርን ለመቅረፍ እንደሚረዳ ገልፀዋል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም ታዳጊው ህፃን ባለበት አካል ጉዳተኝነት ምክንያት ከትምህርት ገበታ መራቅ እንደሌለበት ገልፀው፣ የትምህርት መርጃ መሳሪያዎችን ድጋፍ ለማድረግ እና ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ ትምህርት ቤት እንዲገባ ዩኒቨርሲቲው አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀዋል።

=== # # #===

!

03/08/2026
02/08/2026

Address

Bule
Dila

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dawit wate werera posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category