Jemal ya galeto

Jemal ya galeto ሁሉም ነጋር ለበጎ ነዉ

06/08/2026
25/07/2026
25/07/2026
04/07/2026
04/07/2026
04/07/2026

📢 ደረሰ! ደረሰ!! ደረሰ!!!

እንኳን ለ2019 በጀት ዓመት የንግድ ሥራ ፈቃድ እድሳት በሰላም አደረሳችሁ፤

የተከበራችሁ በዌራ ዲጆ ወረደ የምትገኙ ታማኝ ግብር ከፋይ ነጋዴዎቻችን በሙሉ፦

የ2019 በጀት ዓመት የንግድ ሥራ ፈቃድ እድሳት ከፊታችን ረቡዕ ሐምሌ 01 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በወረዳችን በአንድ ማእከል በበሸኖ ከተማ የኦን-ላይን አገልግሎት መስጫ ጣቢያ ላይ ይሰጣል።

ስለሆነም የተከበራችሁ ግብር ከፋይ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት በሙሉ አገልግሎቱን ለማግኘት
በበሸኖ ከተማ በሚገኘው የንግድና ገበያ ልማት ጽሕፈትቤት በመቅረብ የንግድ ስራ ፈቃዳችሁን በወቅቱ በማሳደስ ንግድዎን በሕጋዊነት ያስቀጥሉ።

የተከበራችሁ ታማኝ ግብር ከፋይ ነጋዴዎች ለፈቃድ እድሳት ሲመጡ የሚያሟሏቸው ቅድመ ሁኔታዎች ወይም መስፈርቶች፦
✔ በእጃችሁ ያለዉን ኦሪጅናል የንግድ ሥራ ፈቃድ፤
✔ የታደሰ ወይም ዲጂታል መታወቂያ፤

✔ ከገቢዎች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የተሰጠ የገቢ ክሊራንስ፤ በክሊራንሱም የ2018 በጀት ዓመት የንግድ ሥራ ትርፍ ግብር መከፈሉን እና ለ2019 በጀት ዓመት የንግድ ሥራ ፈቃዱ እንዲታደስ ተቃውሞ እንደሌለ የሚያረጋግጥ መሆን አለበት፤

✔ ለፈቃድ እድሳት የተወሰነውን 102 (አንድ መቶ ሁለት) ብር የአገልግሎት ክፍያ፤

የዌራ ዲጆ ወረደ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከይሩ እ/ሁሴን "የንግድ ፈቃድዎን በወቅቱ ማደስ ሕጋዊ ግዴታ ብቻም ሳይሆን ለንግድ ቀጣይነት፣ ለተሻለ አገልግሎት እና ለወረደችን ኢኮኖሚያዊ እድገት ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ነጋዴዎች ለእድሳት የሚያስፈልጉትን ሰነዶች በቅድሚያ በማሟላት በተጠቀሰዉ ጊዜ ውስጥ ቀርባችሁ ፈቃዳችሁን በወቅቱ እንዲታሳድሱ በማለት ጥሪ አቅርቧል።

ለዚህም ተቋማችን ፈጣን፣ ቀልጣፋ እና ግልጽ አገልግሎት ለመስጠት ሙሉ ዝግጁነት ላይ ይገኛል ብለዋል።

ማሳሰቢያ
=======
↘️ ሁሉም ነጋዴዎች ከላይ የተጠቀሱትን ሰነዶች አሟልታችሁ በወቅቱ በመቅረብ አገልግሎቱን እንዲያገኙ በአክብሮት እናሳስባለን!!

"ፈቃድዎን በወቅቱ ያድሱ፤ ንግድዎን በሕጋዊነት ያስቀጥሉ!"

የዌራ ዲጆ ወረደ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ።

04/07/2026

ክቡር ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን ሁሴን የዞኑን አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በገመገሙበት ወቅት የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎችን አስቀመጡ
========
ሰኔ 27/2018

የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን የዞኑን አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በገመገሙበት ወቅ ትየቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።

↪️ ቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች የመንግስት ኮማንድ ፖስት አደረጃጀት እስከ ቀበሌ ድረስ መጠናከር ያስፈልጋል።

↪️ በሁሉም ዘርፍ ችግር ፈቺ እቅድ በመቃድ ለተግባራዊነቱ በትኩረት ሰጥተው መስራት እንዳለበት ይጠበቃል።

↪️ የአገልግሎት አሰጣጣችን ከበር መልስ ጀምሮ ሳቢና ለስራ ምቹ ሁኔታዎች መፍጠር ያስፈልጋል።

↪️ በየተቋሙ የሚከናወኑ ተግባራት የህብረተሰቡን ፍላጎት ማሟላት በሚያስችልና ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ ልሆን ይገባል።

↪️ ለአንድ ሀገር መንግስት ግንባታ ህዝብና መንግስት መተማመን ያስፈልጋል ያሉ ስሆን ለዚህም የመንግስት ሰራተኞች የአገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻል ያስፈልጋል።

↪️ የድጋፍና ክትትል አግባብ ማሻሻል ያስፈልጋል ያሉት ስሆን የሚደረገው ድጋፍ ችግር ፈቺ መሆን አለበት።

↪️ በየዘርፉ አዳዲስ ሀሳቦችን ማፍለቅ፣ መልካም ተሞክሮዎችን መቀመርና ማስፋት ይገባል።

↪️ በዞኑ የሚያመነጨውን ገቢ እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ በተገቢው በመሰብሰብ የህብረተሰቡን መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል።

↪️ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር የተጀማመሩ ስራዎች በመጠናከር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት አንስተዋል።

↪️ በከተማ የህገ ወጥ የመሬት ወረራ በመከላከል በተገቢው ሁኔታ መምራት እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።

↪️ የአርሶ አደሩን ህይወት ለመቀየርና ከችግሩም ለመውጣት ተግባራዊ የሆኑ የተለያዩ ኢንሼቲቮችን በተቀናጀ ሁኔታ መሰራት እንዳለበት አስቀምጧል።

↪️ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት በየአካባቢው የሰንበት ገበያን ይበልጥ ማጠናከር ይገባል።

↪️ ህገወጥ የቤንዚል የንግድ እንቅስቃሴ ለመከላከል ከአስተዳደራዊ እርምጃ ባለፈ ህጋዊ እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል።

↪️ በሁሉም መዋቅሮች የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማት ታቅዶ ወደ ስራ በመግባት የተጀመሩ ስራዎች ልዩ ትኩረት መስጠት ይገባል።

↪️ በተለይም ፋይዳ መታወቂያ እና ኢትዮ ኮደሪስ የታቀደው ዕቅድ ግብ መድረስ እንደሚገባ አንስተዋል።

↪️ በየደረጃው ወጥነት ያለው ዕቅድ መታቀድ እንዳለበት አመላክተዋል።

↪️ በቀጣይ በጀት አመት ተግባራት በቅንጅት የሚመሩ መሆኑን ነው ያነሱት።

↪️ የዞኑ አመራሩ እና ታችኛው መዋቅር ከወትሮውም በተለየ መልኩ የህዝብ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የተጀመሩ የለውጥ ስራዎችንም ማስቀጠል ይገባል።

↪️ አመራሩ ከወትሮውም በበለጠ መልኩ ቅንጅትና አንድነቱን አጠናክሮ ማስቀጠል ያስፈልጋል።

↪️ በአጠቃላይ ቀጣይ በበጀት ዓመት ህብረተሰባችን በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገብ ይገባናል ሲሉም ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

Address

Sodo

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jemal ya galeto posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share