19/04/2025
የወላይታ ሶዶ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ እና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፀጋዬ ተ/ሀይማኖት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልክት እንደሚከተለው ይቀርባል ።
አቶ ፀጋዬ በእንኳን አደረሳችሁ መልክታቸው
የደህንነታችን ቤዛ የሆነው ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለሰው ልጆች ሃጢአት ማስተሰርያ ሲል፣ ሥጋዉን ቆርሶ፣ ክቡር ደሙን አፍሦ፣ ሞትን ድል አድረጎ የተነሳበትን የትንሳኤውን በዓል እንኳን በሠላም እና በጤና አደረሳችሁ! አደረሰን ያሉት ኃላፊው የትንሣኤ በዓል በክርስቶስ ፍቅር የሰው ልጅ ከሃጢያት ባርነት ነፃ የወጣበት ሰለሆነ እኛም ትንሳኤ ብርሃኑን ስናከብር ጥላቻን በመተው ፍቅርን በመስበክ በአንድነት ሁነን የተቸገሩትን በማሰብ እና በማገዝ መሆን እንዳለበት በመልዕክታቸው ተናግረዋል።
ትንሳኤ ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰዉ ልጆች ፍቅር መከራውን ሁሉ በፅናት አልፎ፣ ዓመተ ኩነኔን ደምስሶ፣ የሰው ልጅን የዕዳ ደብዳቤ ቀዳዶ፣ ሲኦልን መዝብሮ፣ ሞትን ድል አድርጎ የተነሳበት በዓል ነው በማለት የገለፁት አቶ ፀጋዬ ።
ይህ በዓል እንደሌሎች መንፈሳዊ በዓላት ለመታሰቢያነት እናከብረው ዘንድ የታዘዝነው ብቻ አይደለም፣ ይልቁንም ተምሳሌትነቱን ተከትለን እንድንፈፅመው ሲሉ ገልጸዋል!
በትንሳኤ ብርሃን ድል የተነሳው ጨልሞ የነበረው ተስፋ ነው ያየነው ትንሳኤ የመከባበር፣ የመታዘዝ፣ አንዱ ለሌላው የመስጠት፣ የማካፈል አብሮ መብላትን ለትውልድ ያስተማረ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡
ከልዩነታችን ይልቅ አንድነታችንን የሚያጎሉ እጅግ ብዙ ዕድሎች አሉን! ያሉት አቶ ፀጋዬ እኛ ኢትዮጵያዊያን ለዘመናት የተጋመደና የተሰናሰለ የጋራ ማንነት ያለን ኩሩ ህዝቦች ነን! ለዚህም እንደ ርግብ ንጹህ የሆነ ልብ ሊኖረን ይገባል ብለዋል ፡፡
የአገራችን ትንሳኤም እውን የሚሆነው በፍቅር፣ በይቅር ባይነት፣ አንዳችን ስለሌላችን ዋጋ በመክፈል፤ ከልብ በመነጨ መደጋገፍና አብሮነት ብቻ ነው ሲሉም አብራርተዋል።
በመጨረሻም አቶ ፀጋዬ በአስተላለፉት መልክት ሁላችንም በምንፈጽመው መልካም ተግባር አገራችን ትሻገራለችና ሁልጊዜም ቢሆን አገረን በማሻገርና የነገን ብርሃን እውን ለማድረግ የሚያስችል የመንፈስ ዝግጅት ሊኖረን ይገባል ስሉ የተናገሩት የመንግሥት ዋና ተጠሪው የዘንድሮው የትንሳኤ በዓል የቆዩ የተሳሳቱ ትርክቶችን በማረም፣ የገዥ ትርክት በማብዛት፣ የለማችና የበለጸገች ሀገርን ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ እኔነትን ሳይሆን እኛነትን መልመድ የግድ በማድረግ ፓርቲያችን ብልጽግና ላለፉት የለውጥ ዓመታት ህልም የመሰሉ በርካታ ድንቅ ስራዎች ማስመዝገብ የቻለ እና ነገን አስቦ ዛሬ ላይ ህዝብን አስተባብሮ እየሰራ የሚገኝ ጠንካራ ፓርቲ መሆኑን እጅ ለእጅ በመያያዝ እናስቀጥል ብዋል።
መልካም የትንሣኤ በዓል
አቶ ፀጋዬ ተ/ሀይማኖት
የወላይታ ሶዶ ከተማ ብልፅግና ፖርቲ ቅ/ቤት ኃላፊ
ሚያዝያ 11/2017
ወላይታ ሶዶ፣