29/10/2025
ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የዜጎችን ሁለንተናዊ ሰላምና ደህንነትን ለማረጋገጥ ጠቀሜታው የጎላ ነው፦ ረዳት ፕሮፌሰር ዘገዬ ጳውሎስ
ወላይታ ሶዶ ጥቅምት 19/2018 ዓ.ም
የወላይታ ሶዶ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የመንግሥት ዋና ተጠሪ ረዳት ፕሮፌሰር ዘገዬ ጳውሎስ፣ እንደገለጹት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ “የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የዜጎችን ሁለንተናዊ ሰላምና ደህንነትን ለማረጋገጥ ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ ሁሉም የህብረተሰቡ ክፍል የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል በቁርጠኝነት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ፋይዳ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን ከሃገራዊ ትልሞቻችን ጋር ተናባቢ ዕሳቤ እንዳለውና ይሄንንም ትልም ዕውን ለማድረግ ሀሉም ባለድርሻ አካላት በሙሉ አቅም መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።
ፋይዳ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ዕድገትና ለዘመነ አገልግሎት አሰጣጥ አስቻይ ከሆኑ መሰረቶች ውስጥ ዋነኛው መሆኑን የገለጹት ኃላፊው በምዝገባ ሂደት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በፍጥነት በማረም የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት በቅንጅት መረባረብ እንደምገባም አንስተዋል።
በመጨረሻም እስካሁን በተግባር አፈጻጸም ሂደት ያጋጠሙትን ተግዳሮቶች በፍጥነት በማረም የተቀመጠውን ከተማዊ ግብ ለማሳካት በልዩ ትኩረት መከወን እንደሚገባም ጠቅሰዋል።
Wolaita S**o City Prosperity Party Branch Office