09/07/2026
ኢትዮጵያ በምክክር ችግሮቿን ትፈታለት ! አዲስ አበባም እንደ መዲናነቷ ታዳሚያንን ተቀብላ በብቃት ለማስተናገድ ዝግጅት አድርጋለች!
ታሪካዊው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሊካሄድ 6 ቀናት ብቻ ቀሩት!
የሀሳብ የበላይነት ሲከበር ፣ መደማመጥ ሲዳብር ሀሳብ አልባነት ቦታ ያጣል። ኢትዮጵያ በብሔራዊ ምክክር በኩል የውይይት ባህልን ለመገንባት ብርቱ ጥረት ጀምራለች።
ከሰሜን ጫፍ እስከ ደቡብ ጫፍ ፣ ከምዕራብ ጫፍ እስከ ምስራቅ ጫፍ ህዝባችን አሉኝ የሚላቸውን ጥያቄዎች በሰለጠነ መንገድ አቅርቧል።
በህዝብ የተነሱ ሁሉንም ጥያቄዎች ሲያሰባስብ የቆየው ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ስምንት ጥቅል አጀንዳዎችን በመጠመር ሀምሌ 8 / 2018 ዓ.ም ሁሉም የህበረተሰብ ክፍል በተወካዮቹ በኩል የሚሳተፍበትን የምክክር መድረክ ደግሷል።
የሁሉም ኢትዮጵያዊ ቤት፣ የአፍሪካ ኩራት፣ የዲፕሎማቲክ ስዕበት የሆነችው መዲናችን አዲስ አበባም ከሁሉም የኢትዮጵያ ወረዳዎች የሚመጡ እንግዶችን መቀበል ጀምራለች፡፡
ይህ የምክክር እና የውይይት አካሄድ አሻጋሪ ነው ። ይህ አካሄድ የሀገራችንን ሁለንተናዊ ብልፅግናን የማረጋገጥ ጉዞን በፅኑ አለት ላይ የሚገነባ ብቸኛው መንገድ ነው።
የሀገራችን ውስብስብ ችግሮች የሚቀረፉት በዳበረ የውይይት ባህል ነው ፤ ከጫፍ እስከ ጫፍ ሁሉንም እያሳተፈ የሚገኘው ብሔራዊ ምክክር ደግሞ አንደኛው ቁልፍ ነው።
ለሀገራችን ብሩህ ተስፋ የፈነጠቀውን ይህ እድል የሰመረ እንዲሆን ሁሉም ዜጋ የድርሻው ጠጠር ሊያሳርፍ ይገባል።
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት