Banding and Landings

Banding and Landings Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Banding and Landings, Grocers, Istanbul.

የመደመር ፍልስፍና መሰረታዊ መነሻ የሰው ልጆችን ፍላጎትና አቅም መዳሰስ ነው። የመደመር ፍልስፍና የፖለቲካ ወይም የኢኮኖሚ ንድፈ-ሀሳብ ብቻ አይደለም፤ መሰረቱ ጥልቅ የሆነ የሰዉ ልጅ አቅምና...
06/03/2026

የመደመር ፍልስፍና መሰረታዊ መነሻ የሰው ልጆችን ፍላጎትና አቅም መዳሰስ ነው።

የመደመር ፍልስፍና የፖለቲካ ወይም የኢኮኖሚ ንድፈ-ሀሳብ ብቻ አይደለም፤ መሰረቱ ጥልቅ የሆነ የሰዉ ልጅ አቅምና ፍላጎት ላይ ያተኮረ ስነ-ልቦናዊና ማህበራዊ እይታ ነው። ማንኛውም ለውጥ ወይም እድገት ስኬታማ የሚሆነው የሰውን ልጅ ውስጣዊ ፍላጎት ሲረዳና ያለውን አቅም ማውጣት ሲችል ብቻ ነው፡፡

የሰው ልጅ ፍላጎቶች ዘርፈ ብዙ ናቸው። ከመሰረታዊ የቁሳቁስ ፍላጎቶች ምግብና መጠለያ ጀምሮ እስከ ስነ-ልቦናዊ ፍላጎቶች ማለትም ክብር፣ እውቅና እና ነፃነት ድረስ ይዘልቃሉ። መደመር እነዚህን ፍላጎቶች በሁለንተናዊ መልኩ በመዳሰስ ያልተመለሱ የትውልድ ጥያቄዎችን ለመመለስ ይተጋል። ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ማሻሻልን ዓላማ ያደርጋል።

እያንዳንዱ ሰው፣ ማህበረሰብም ሆነ ሃገር የራሱ የሆነ ፀጋና አቅም አለው። መደመር ይህንን አቅም አቀናጅቶ መጠቀምን ያስተምራል፡፡ ያሉንን መልካም እሴቶች በመጠበቅ፣ ጉድለቶቻችንን ደግሞ በሌላው አቅም በመሙላት ወደ ላቀ ውጤት እንድንሸጋገር ያግዘናል። የሰው ሀብትን ወደ ምርታማነት በመቀየር የብልፅግና ጉዞን ያፋጥናል።

የሰው ልጅ ፍላጎቱና አቅሙ ሲጣጣም ውጤቱ ሰላም፣ ልማትና ዴሞክራሲ ይሆናል፡፡ መደመር የቆዩ ስብራቶችን በመጠገን እና አዳዲስ አቅሞችን በመገንባት፣ የሁላችንንም ፍላጎት የምታስተናግድ ጠንካራ ኢትዮጵያን ለመገንባት ዋና ግብ አድርጎ ይሰራል።

ሁላችንም ልክ እንደ ስንዴ ነዶ በአንድነት ቆመን፣ በያለንበት ዘርፍ የሌላውን ፍላጎት እያከበርን፣ የራሳችንን አቅም ደግሞ ለጋራ እድገት ስናበረክት "መደመር" ትርጉም ይኖረዋል።

14/11/2025

የጡት ካንሰር - ይወቁ፣ ይቅደሙ!

1. የጡት ካንሰር ምንድን ነው?

የጡት ካንሰር በጡት ውስጥ ያሉ ሕዋሶች ባልተለመደ መልኩ ሲራቡና ሲያድጉ የሚከሰት በሽታ ነው። የጡት ካንሰር በኢትዮጵያ የተስፋፋ ያለ የካንሰር ዓይነት ሲሆን፣ ከሁሉም የካንሰር አይነቶች የጡት ካንሰር ታማሚዊች 32% ይዞ ይገኛል።

መረጃዎች እንደሚያሣዩት በየዓመቱ 16,000 በላይ አዲስ የጡት ካንሰር ታማሚዎች በኢትዮጲያ ይመዘገባሉ። ከ70% በላይ ሴቶችም በሽታው የመጨረሻ ደረጃ ወይም ስር ከሰደደ በሁዋላ ወደ ጤና ተቋም ስለሚመጡ የህክምናው ዉጤት ዉስብስብ እና ዝቅተኛ ያደርገዋል፡፡ በኢትዮጵያ አብዛኛው ሴቶች የጡት ካንሰር ግንዛቤ ስለሌላቸዉ የምርመራ እና የሕክምና አገልግሎቶች ለማግኘት የተገደቡ ናቸው።

2. የጡት ካንሰር በምን ይከሰታል?

የጡት ካንሰር አንድ የተለየ መንስኤ ባይኖረዉም፤ መከላከል የምንችላቸዉ እና የማንችላቸዉ ነገሮች በምክንያትነት ይጠቀሳሉ።

3. መነሻ ምክንያቶች

• በቤተሰብ የነበረ ታሪክ ወይም የተወረሰ ዘረመል
• የመጀመሪያ የወር አበባ ቀደም ብሎ መጀመር ወይም ለማረጥ መዘግየት እና እድሜ መጨመር
• የመጀመሪያ እርግዝናን ከ30 ዓመት በኋላ ሲሆን እና አለማጥባት
• ወፍረት፣ በተለይ የወር አበባ ከተቋረጠ በኋላ
• አልኮል መጠጣት ወይም ማጨስ
• ቀደም ብሎ በደረት ላይ የተደረገ የጨረር ሕክምና ጋር ተያይዞ መኖር መንስኤዎች ሊሆኑ ይችላሉ።

4. ምልክቶች — ከሚከተሉት አንዱን ካዩ ወደ ጤና ባለሙያ ይሂዱ!

• በጡት ወይም በእጅ ትከሻ ስር የተለየ እብጠት ወይም መጠጠር
• የጡት መጠን ወይም ቅርፅ መቀየር
• የቆዳ መቅላት ወይም መንቀጥቀጥ
• የጡት ጫፍ ወደ ውስጥ መግባት ወይም ደም የያዘ ፈሳሽ መውጣት
• በጡት ውስጥ በአንድ ቦታ የማያቆም ህመም መሰማት ምልክቶች ናቸው።

5. በቀላሉ ራስዎን መፈተሻ መንገድ

1. በመስታወት ፊት ቆሞ ትከሻዎን ቀጥ በማድረግ እና እጆችዎን በወገብ ላይ አድርገው ጡቶችዎን ይመልከቱ። የቆዳ መቆጣት እና የጡት መጠን ለውጦች ይመልከቱ። እጆችዎን ወደ ላይ ቀጥ አድርገው ያንሱ እና ለውጦችን ይመልከቱ።
2. በተጨማሪ አንድ እጅዎን በማንሳት በሌላኛው እጅዎ በመካከለኛው 3 ጣቶች ክብ እንቅስቃሴ በማደረግ ከጡትዎ የውጨኛ ክፍል ጀምረው እስከ ጫፉ ድረስ ይመርምሩ። እጅዎን በመቀያየር ሁለቱንም ጡቶች ተኝተው አልያም ቆመው መመርመር ይችላሉ።

6. ምርመራ

• ከላይ የተጠቀሱ ምልክቶችን ካስተዋሉ እና የተለየ ለውጥ ካገኙ በፍጥነት ወደ ጤና ተቋም በመሄድ ምርመራ ያድርጉ።
• የጡት ካንሰር ምርመራ በሰለጠነ የጤና ባለሙያ በተመረጡ ጤና ተቋማት ይሰጣል።
• የጡት ካንሰር ምርመራ እንደ አስፈላጊነቱ አልትራሳውንድ ወይም ማሞግራፊ ጨምሮ ፓቶሎጂ ምርመራዎችን ያጠቃልላል።

7. ሕክምና

የጡት ካንሰር ህክምና የተለያዩ አማራጮች አሉት
• ቀዶ ጥገና፣ ኬሞቴራፒ፣ የሆርሞን እና የጨረር ሕክምና

8. ተጋላጭነትን ለመቀነስ መደረግ ያለባቸው ነገሮች

• ክብደት መቆጣጠርና አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ
• አልኮልን መቀነስ እና አለማጨስ
• በተቻለ መጠን በወሊድ ወቅት ማጥባት
• በቤተሰብ ውስጥ የበሽታው ታሪክ ካለ ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ ምርመራ ማድረግ
• ማንኛውም ለውጥ በሚኖርበት ጊዜ ቀደም ብለው ህክምና ምርመራ ያድርጉ — ቀድሞ ከተገኘ የመዳን እድሉ ከፍተኛ ስለሆነ

9. መቼ ወደ ህክምና ተቋም መሄድ አለብዎት

ያልተመደ እብጠት ወይም መጠጠር፣ የቆዳ ለውጥ፣ የጡት ጫፍ ለውጥ ወይም የጡት ህመም ሲያጋጥምና ምልክቶቹ ከጥቂት ሳምንታት በላይ ከቆዩ በአፋጥኝ ወደ ጤና ተቋም በመሄድ ምርመራ ማድረግ ያስፈልጋል።

ቀደም ብሎ መገንዘብ ሕይወትን ያድናል - ጡቶችዎን ይመርምሩ፣ ለማንኛውም ለውጥ ወደ ጤና ተቋም ይሂዱ።

ለበለጠ መረጃ በነፃ የስልክ መስመር #952 ይደውሉ!



Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

15/08/2025
15/08/2025
16/05/2025

በወቅታዊ የጤና አገልግሎት ዙሪያ ከጤና ሚኒስቴር የተሰጠ መረጃ
*****************

የጤና ሚኒስቴር ለማኅበረሰባችን ጥራቱን የጠበቀ እና ፍትሐዊ የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የጤና ፖሊሲ እና ስትራቴጂ በመቅረጽ የኅብረተሰቡን ባለቤትነት ባረጋገጠ መልኩ ሥራዎችን በትኩረት እያከናወነ መሆኑ የዐደባባይ ሐቅ ነው።

ምክንያቱም መቼምና በምንም ሁኔታ መቋረጥ ከሌለባቸው ማኅበራዊ አገልግሎቶች አንዱ የጤና አገልግሎት በመሆኑ፤ ስለዚህም ዛሬን ጨምሮ ባለፉት ቀናት በመላ ሀገራችን በሚገኙ የጤና ተቋማት እንደ ወትሮው ሁሉ መደበኛ የጤና አገልግሎቶች ለማኅበረሰባችን ያለምንም መቆራረጥና መስተጓጎል እየተሰጡ ይገኛሉ።

ይሄንን የተረዳው የጤና ባለሞያ በማኅበራዊ ሚዲያ በሚሠራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች ጫና ሳይገፋ የገባውን የሞያ ቃል ኪዳን እና መሐላ ጠብቆ ማኅበረሰቡን እያገለገለ በመሆኑ ምስጋና ይገባዋል።

ይሁን እንጂ በጥቂት የማስተማሪያ የጤና ኮሌጆች/ተቋማት በመደበኛ የሥራ ገበታቸው ላይ ያልተገኙ የተወሰኑ ባለሞያዎች እንዳሉ መረጃዎች ደርሰውናል። ከእነዚህ የጤና ባለሞያዎች መካከል ብዙዎቹ በሐሰተኛ መረጃ የተወናበዱ ሲሆኑ ጥቂቶቹ ደግሞ ጥፋትን ዓላማቸው ያደረጉ ናቸው።

ድርጊቱ የራስን ቤተሰብ፣ ዘመድ፣ ወገን እና መላውን ማኅበረሰብ ከመጉዳት ባለፈ ከሞያ ሥነ ምግባር፣ ከሰብአዊነት አኳያ ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው።

ከሕግ አኳያም የጤና ሞያ የሥራ ማቆም አድማ ከማይደረጉባቸው የሥራ ዘርፎች መካከል አንዱ መሆኑ በግልጽ ተደንግጓል። የጤና ባለሞያዎች ጥያቄ እንኳን ቢኖራቸው በሥራ ገበታቸው ተገኝተው መደበኛ ሥራቸውን እያከናወኑ ጉዳያቸውን ለሚመለከተው አካል ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።

በመሆኑም እነዚህ የጤና ባለሞያዎች ወደ ሥራ ገበታቸው ተመልሰው ማኅበረሰባቸውን እንዲያገለግሉ በየተቋማቸው ጥሪ ተደርጓል።

መንግሥት የጤና ባለሞያውን ዘላቂ ተጠቃሚነት ባረጋገጠ መልኩ በጥናት ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ለመስጠት ቀደም ብሎ የጤና አገልግሎት አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ 1362 /2017 አጸድቆ ደንብና መመሪያዎችን በማውጣት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል።

በጎ ኅሊና ያላቸው የጤና ባለሞያዎች ይህንን በመገንዘብ ሥራቸውን በአግባቡ እንዲያከናውኑ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤታችን በዚሁ አጋጣሚ ጥሪ ያቀርባል።

በሌላ በኩል ደግሞ ኅብረተሰቡ በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች በሚሠራጩ የሐሰት መረጃዎች ሳይረበሽ የሚፈልገውን የጤና አገልግሎት በተለመደው መልኩ በጤና ተቋማት ማግኘት እንደሚችል እናሳውቃለን።

መንግሥት በሆደ ሰፊነት ችግሩን ለመፍታት ያሳየውን ትዕግሥት ወደጎን በመተው በሥራ ገበታቸው ላይ ባልተገኙ እንዲሁም በጤና ተቋሙም ሆነ ከጤና ተቋሙ ውጭ ሆነው ሁከትና ብጥብጥ በሚፈጥሩት ላይ አስፈላጊ የሆነ ሕጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ቀድመን እናሳውቃለን።

የጤና ሚኒስቴር
ግንቦት 07፣ 2017 ዓ.ም

16/05/2025

Address

Istanbul

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Banding and Landings posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category