16/02/2026
ከሠላት የቀጠለ
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 40, ሐዲስ 13
ጃቢር እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "በኢማን እና በኩፍር መካከል የሚለየው ሶላት ነው"። عَنْ جَابِرٍ، أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ بَيْنَ الْكُفْرِ وَالإِيمَانِ تَرْكُ الصَّلاَةِ
ከነቢያችን”ﷺ” በፊት በነበሩት ነቢያት በቀን አምስት ጊዜ ሶላት ላይቆሙ ይችላሉ፥ ወይ ያንሳል አሊያም ይበዛ ይሆናል። ነገር ግን አሏህ ሶላትን መስገድ ወደ እነርሱ አውርዷል፦
21፥73 ”ወደ እነርሱም መልካም ሥራዎችን መሥራትን፣ ሶላትንም መስገድን፣ ዘካንም መስጠትን አወረድን”፡፡ وَأَوْحَيْنَآ إِلَيْهِمْ فِعْلَ ٱلْخَيْرَٰتِ وَإِقَامَ ٱلصَّلَوٰةِ وَإِيتَآءَ ٱلزَّكَوٰة
"ፈሕሻእ" فَحْشَاء ማለት "መጥፎ ቃላት" ማለት ሲሆን "ሙንከር" مُنكَر ደግሞ "መጥፎ ሥራ" ነው፥ ሁለቱም የሸይጧን እርምጃዎች ናቸው። ሶላት ግን በኢማን፣ በኢኽላስ እና በኢትባዕ ከተፈጸመች ከፈሕሻእ እና ከሙንከር ነገር ሁሉ ትከለክላለች፦
24፥21 እርሱ በመጥፎ እና በሚጠላ ነገር ያዛልና፡፡ فَإِنَّهُ يَأْمُرُ بِالْفَحْشَاءِ وَالْمُنكَرِ
29፥45 ሶላት ከመጥፎ እና ከሚጠላ ነገር ሁሉ ትከለክላለችና፡፡ አላህንም ማውሳት ከሁሉ ነገር በላጭ ነው። إِنَّ الصَّلَاةَ تَنْهَىٰ عَنِ الْفَحْشَاءِ وَالْمُنكَرِ ۗ وَلَذِكْرُ اللَّهِ أَكْبَرُ
ሶላት በዱንያህ የምታስረዳ እና አሏህ በሚፈሩት ላይ ቀላት ናት፥ በአኺራ ደግሞ የጀናህ ቁልፍ ናት፦
2፥45 በመታገስ እና በሶላትም ተረዱ! እርሷም (ሶላት) በፈሪዎች ላይ እንጅ በሌላው ላይ በእርግጥ ከባድ ናት፡፡ وَاسْتَعِينُوا بِالصَّبْرِ وَالصَّلَاةِ ۚ وَإِنَّهَا لَكَبِيرَةٌ إِلَّا عَلَى الْخَاشِعِينَ
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 4
ሙጃሂድ እና ጃቢር ኢብኑ ዐብደሏህ"ረ.ዐ." የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ሶላት የጀናህ ቁልፍ ናት፥ ውዱእ ደግሞ የሶላት ቁልፍ ነው"። عَنْ مُجَاهِدٍ، عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ، رضى الله عنهما قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " مِفْتَاحُ الْجَنَّةِ الصَّلاَةُ وَمِفْتَاحُ الصَّلاَةِ الْوُضُوءُ "
አሏህ ሙሶሊን ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
ወሠላሙ ዐለይኩም