06/09/2026
እናቱ የዓምዕሮ ህመምተኛ አባት ጥበቃ ስለሆኑ ቀኑን ሙሉ ቤት ተቆልፎበት የሚዉለዉ ህፃን ዉጪ ለማየት ያለዉን ጉጉት
ነገሩ የሆነዉ በነገሌ ቦረና የከብቶች ገበያ ሰፈር አከባቢ መሆኑን ግዮን ማለዳ አረጋግጧል ። ይህን ምስል ያጋራዉ ሰዉ ድንገት በዚያ ሲያልፍ አይኑ ድንገት አንድ በተቆለፈ በር ስር አጮልቆ ወደ ዉጪ የሚመለከት ታዳጊ ላይ ያርፋል።
የሚያየዉን ማመን አቃተዉ በትልቅ ድንጋየይ ስር አጮልቆ ዉጪዉን ይመለከታል።እየተራመደ ወደ በሩ ሲጠጋ በሩ ተቆልፎአል።
ጎረቤት ያሉ ሰዎችን ሲያናግር እናቱ የአእምሮ ህመምተኛ ነች አባቱ ደግሞ የዘበኝነት ስራ ስለሚሰራ ለሊት ወጥቶ ማታ ነዉ የሚመጣዉ ህፃኑ ብቻዉን ተቆልፎበት ቤት ዉስጥ ነዉ የሚዉለዉ እዛዉ ነዉ የሚፀዳዳዉ፣በጣም የሚያሳዝነዉ ደሞ እራቁቱን ነዉ።
ሕፃናት የማንም የግል ጉዳይ ብቻ አይደሉም። ተጨማሪ ፎቶዎች የፈስቡክን ህግ ስለሚጥሱ በ Ghion Maleda ቴሌግራም ቻናል ላይ ይመልከቷቸው ። እጅግ ልብ ሰባሪ ነው። ማንኛውም ሕፃን በአደገኛ ሁኔታ ውስጥ ከተገኘ ጎረቤት፣ ማህበረሰብና ተቋማት ተባብረው ደህንነቱን ማረጋገጥ ይገባል። ፍትህ ሊያገኝ ይገባል !
እናትና አባትን በመውቀስ ብቻ ሳይሆን መፍትሄ እንፈልግ። ከቤተሰቡ ችግር በስተጀርባ የአእምሮ ጤና፣ የኢኮኖሚ ችግር ወይም ሌሎች ሁኔታዎች ሊኖሩ ስለሚችሉ የቤተሰቡ ድጋፍም አስፈላጊ ነው።
አንድ ሕፃን ከበር ስር አጮልቆ የውጭውን ዓለም ሲመለከት ማየት ብቻ አያስፈልገንም፤ የሚፈልገውን እርዳታ እንዲያገኝ እንርዳው።
ሕፃናት መብታቸው ነው በደህና መኖር፣ መጫወት እና የውጭውን ዓለም በነፃነት ማየት። 🙏💔
እባካችሁ ለደጋጎች ይሄ መልዕክት እንዲደርስ #ሼር በማድረግና መረጃውን በማጋራት አድርሱልን የኛ አንድ የህፃኑን ህይወት ሊለውጥ ይችላል
ግዮን ማለዳ
ቅኔ ሚዲያ