Amhara RoadTransport and Logistics Bureau

Amhara RoadTransport and Logistics Bureau ፕሮጀክት ላንጨረስ አንጀምርም !!

በአርጡማ ፋርሲ ወረዳ የመንገድና የድልድይ ግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ተገመገመ፡፡*******ከሚሴበአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር በአርጡማ ፋርሲ ወረዳ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ...
18/06/2026

በአርጡማ ፋርሲ ወረዳ የመንገድና የድልድይ ግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ተገመገመ፡፡
*******
ከሚሴ
በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር በአርጡማ ፋርሲ ወረዳ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች የመስክ ምልከታና የጋራ የግምገማ መድረክ ተካሂዷል።

በመስክ ጉብኝቱ ላይ የጨፋ-ቂጪጮ-ሀራ የመንገድ ፕሮጀክት እና የዲምቱ ቀበሌ የኮንክሪት ድልድይ ግንባታ የስራ እንቅስቃሴ በቦታው ተገኝቶ የተገመገመ ሲሆን፥ የፕሮጀክቶቹ አጠቃላይ አፈጻጸም በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።

በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መንገድና ትራንስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መሐመድ ሲራጅ ሙስጠፋ እና የገንዘብ መምሪያ ኃላፊ አቶ አብዱ ሙሄን ጨምሮ ሌሎች የዞንና የወረዳ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ባለሙያዎች እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቶቹ የተቀመጠላቸውን ጥራት ጠብቀውና በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ ተጠናቀው ለሕዝብ አገልግሎት እንዲበቁ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።

ከመስክ ምልከታው ማጠናቀቂያ በኋላ ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ የምክክር መድረክ የተካሄደ ሲሆን፥ በውይይቱም የፕሮጀክቶቹን አጠቃላይ አፈጻጸም በመገምገም፣ በቀሪ ጊዜያት መከናወን ባለባቸው ወሳኝ ተግባራትና ሊወሰዱ በሚገባቸው መፍትሄዎች ዙሪያ ግልጽ አቅጣጫ መቀመጡን ከዞኑ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

የጎንደር ከተማ ከመሠረት ትምህርት ቤት እስከ አውቶ ፓርክ ድረስ የአስፋልት ንጣፍ ሥራ እየሰራ ነው። አስፓልት ንጣፍ ስራው የኮሪደር  ልማቱ አንዱ አካል ሲሆን የከተማዋን የመንገድ መሠረተ ል...
18/06/2026

የጎንደር ከተማ ከመሠረት ትምህርት ቤት እስከ አውቶ ፓርክ ድረስ የአስፋልት ንጣፍ ሥራ እየሰራ ነው።

አስፓልት ንጣፍ ስራው የኮሪደር ልማቱ አንዱ አካል ሲሆን የከተማዋን የመንገድ መሠረተ ልማት የበለጠ ለማስዋብ ያለመ ነው። በአሁኑ ወቅት የአስፋልት ንጣፍ ሥራው በጥራት እየተሰራ ይገኛል።

የደባርቅ - ቧሂት አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታን ለማፋጠን ሰፊ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታወቀ።****​በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን የሚገኙትን...
18/06/2026

የደባርቅ - ቧሂት አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታን ለማፋጠን ሰፊ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታወቀ።
****
​በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን የሚገኙትን የደባርቅ እና የጃናሞራ ወረዳዎችን ከበየዳ ወረዳ ጋር የሚያገናኘው ይህ ታላቅ የመንገድ ፕሮጀክት፣ በአጠቃላይ 63 ነጥብ 21 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍን ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግንባታው በጥሩ ፍጥነት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።

​የመንገድ ፕሮጀክቱ ጅማሮውን ደባርቅ ከተማ ላይ አድርጎ እስከ ቧሂት ከተማ ድረስ የሚዘልቅ ሲሆን፣ ግንባታው በከተማ 19 ሜትር፣ በወረዳ ማዕከላት 20.5 ሜትር እንዲሁም በገጠር 7 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል።

​ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ የሚሆን 4,174,470,239.57 (አራት ቢሊዮን አንድ መቶ ሰባ አራት ሚሊዮን አራት መቶ ሰባ ሺህ ሁለት መቶ ሰላሳ ያኝ ብር ከሃምሳ ሰባት ሳንቲም) በጀት የተመደበ ሲሆን፣ ወጪው ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት የሚሸፈን ነው። ታላቁን የግንባታ ስራ የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ እያከናወነው ሲሆን፣ የግንባታውን ጥራት የመቆጣጠርና የማማከር ስራውን ደግሞ አይ.ዲ.ኮን ኢንፍራስትራክቸር ዴቨሎፕመንት ኮንሰልታንትስ ኃ.የተ.የግ ማህበር በኃላፊነት ይዞ እየሰራው ይገኛል።

​በአሁኑ ወቅት በፕሮጀክቱ ላይ የአስፓልት ማንጠፍ፣ የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ የድሬኔጅ (የውሃ ማፍሰሻ)፣ የሰብ ቤዝ እና የቤዝ ኮርስ ስራዎች በተጠናከረ መልኩ እየተከናወኑ ነው። ከዚህ በተጨማሪም የቤዝ ኮርስና የአስፓልት ኮንክሪት ጠጠር መፍጨት፣ የፓይፕ ማምረት እንዲሁም በርካታ የስትራክቸር (የማጠናከሪያ) ስራዎች በመሰራት ላይ መሆናቸውን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር መረጃ ያመላክታል።

​የዚህ መንገድ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ መገንባት ለአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ለትራንስፖርት መስመሩ ተጠቃሚዎች ዘርፈ-ብዙ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞችን እንደሚያስገኝ ተመልክቷል። በተለይም ቀደም ሲል በተሽከርካሪ ለመጓዝ 4 ሰዓት ገደማ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ብቻ በማሳጠር የህዝቡን የትራንስፖርት እንግልት በእጅጉ ይቀንሰዋል።

​መንገዱ ለአካባቢው አርሶ አደሮችም ትልቅ እፎይታን የሚሰጥ ሲሆን፣ ያመረቱትን የግብርና ምርት ካለምንም ችግር በአፋጣኝ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማውጣት አምራችና ሸማቹን በቀላሉ ለማገናኘትና ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ያስችላል። ከዚህ ባለፈም የሰሜን ብሔራዊ ፓርክን ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች ይበልጥ ምቹ በማድረግ የቱሪዝም ፍሰቱን የሚያሳድግ ሲሆን፣ ወደ አካባቢው የሚመጣውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በመሳብ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ ይጠበቃል።

በላይ ጋይንት ወረዳ የ 4 ሰዓቱን የእግር ጉዞ ወደ 30 ደቂቃ የሚያሳጥረው የመንገድ ግንባታ በተፋጠነ ሁኔታ እየተከናወነ ነው!***[ላይ ጋይንት] — በደቡብ ጎንደር ዞን በላይ ጋይንት ወረዳ...
16/06/2026

በላይ ጋይንት ወረዳ የ 4 ሰዓቱን የእግር ጉዞ ወደ 30 ደቂቃ የሚያሳጥረው የመንገድ ግንባታ በተፋጠነ ሁኔታ እየተከናወነ ነው!
***
[ላይ ጋይንት] — በደቡብ ጎንደር ዞን በላይ ጋይንት ወረዳ ለዘመናት የአካባቢው ማህበረሰብ የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበረው የ 12.2 ኪሎሜትር የጎብጎብ - የጥጆ - ሀገረ ገነት ደረጃ ሁለት የጠጠር መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና ስራው በተፋጠነ ሁኔታ እየተሰራ መሆኑን የወረዳው መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ጽ/ቤት አስታወቀ።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ደረጀ ሞላ እንደገለጹት፤ መነሻውን ጎብጎብ ከተማ አድርጎ እስከ የጥጆ ማርያም ድረስ የሚዘልቀውን ይህንን ወሳኝ የመንገድ ፕሮጀክት በተቀመጠለት አጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የ 6 ኪሎ ሜትር የግንባታ ስራ በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

💰 በህዝብና በነዋሪው ጥምረት የፈሰሰ በጀት
ለዚህ ግዙፍ የልማት ስራ ማስፈጸሚያ የሚውለው 13 ሚሊዮን ብር ሲሆን፣ የበጀት ምንጩም የመንግስትንና የህዝብን ትብብር በሚያሳይ መልኩ የተቀረጸ ነው፦

10 ሚሊዮን ብር፦ በወረዳው ምክር ቤት የተሸፈነ፣

3 ሚሊዮን ብር፦ በቀጥታ በማህበረሰቡ ተሳትፎ የተሰበሰበ ነው።

🚜 የመንገዱ ስታንዳርድ እና የሚያስተሳስራቸው አካባቢዎች
ይህ ባለ 6 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ደረጃ ሁለት የጠጠር መንገድ ግንባታ ሲጠናቀቅ፤ ጎብጎብና ሀገረ ገነት ከተሞችን ከማስተሳሰሩም በላይ በመስመሩ ላይ የሚገኙ አራት የገጠር ቀበሌዎችን በቀጥታ ተጠቃሚ ያደርጋል።

💡 ለጤናና ለኢኮኖሚ እድገት የላቀ ፋይዳ
መንገዱ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ መገንባቱ በአካባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ አዲስ ምዕራፍ ይከፍታል ተብሏል። አቶ ደረጀ ሞላ የመንገዱን ዋና ዋና ጥቅሞች ሲዘረዝሩ፡

የህይወት አድን አገልግሎት፦ ለወላድ እናቶች የአምቡላንስ አገልግሎትን ፈጣንና ተደራሽ ያደርጋል።

የገበያ ትስስር፦ በአካባቢው በስፋት የሚመነጩና የሚመረቱትን እንደ አሸዋ፣ ባህር ዛፍ፣ ድንች፣ ስንዴ እና ባቄላ ያሉ ምርቶችን ያለእንግልት፣ በሰዓቱና በደህንነቱ በተጠበቀ ትራንስፖርት ወደ ገበያ ለማቅረብ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።

⏱️ ከ 4 ሰዓት ወደ 30 ደቂቃ!
ከዚህ ቀደም ነዋሪዎች በእግር ለመጓዝ ይገደዱበት የነበረውንና 4 ሰዓት ይፈጅ የነበረውን አድካሚ ጉዞ ወደ 30 ደቂቃ ብቻ እንደሚያሳጥረው የተገለጸ ሲሆን፣ ይህም የትራንስፖርት ተጠቃሚዎችን አላስፈላጊ እንግልት ሙሉ በሙሉ የሚያቃልልና የከተሞችን እድገት የሚያፋጥን መሆኑ ተጠቁሟል።

የአካባቢው ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት፤ መንገዱ የረጅም ጊዜ የልማት ጥያቄያቸው የነበረ በመሆኑ አሁን ላይ በተግባር ተጀምሮ በጥሩ ሁኔታ ላይ መገኘቱ ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረባቸውና ለስኬታማነቱም ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

[የላይ ጋይንት ኮሙኒኬሽን — ሰኔ 9/2018 ዓ.ም]

በትራንስፖርት ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ፡ የኢትዮጵያን ኮድ “ETH” ያካተቱ ዘመናዊና ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ አዳዲስ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳዎች (ታርጋዎች) ሊስተዋወቁ ነው፡፡****አዲስ...
16/06/2026

በትራንስፖርት ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ፡ የኢትዮጵያን ኮድ “ETH” ያካተቱ ዘመናዊና ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ አዳዲስ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳዎች (ታርጋዎች) ሊስተዋወቁ ነው፡፡
****
አዲስ አበባ — የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በትራንስፖርት ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍ እና የተሽከርካሪዎችን ደኅንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ የሚያስችል፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመለት አዲስ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ (ታርጋ) እና ስቲከር አገልግሎት ላይ ሊያዉል መሆኑን አስታወቀ።

ይህ አዲስ አሰራር ቀደም ሲል የነበሩ የተሽከርካሪ ምዝገባዎችን እና የሰነዶችን ህጋዊነት በማረጋገጥ በድጋሚ ለመመዝገብ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል።

ዓለም አቀፍ ደረጃ እና ወጥነት
አዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሥርዓት የቪየና ስምምነትን (Vienna Convention) መነሻ ያደረገ ሲሆን፣ በደረጃ፣ በመጠን እና በንድፍ (ዲዛይን) ወጥነት እንዲኖረው ተደርጎ ተቀርጿል። ትልቁ ማሻሻያ በሰሌዳው ላይ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ መለያ ኮድ “ETH” ማካተት መቻሉ ሲሆን፣ ይህም ለእያንዳንዱ ተሽከርካሪ ልዩ የሆነ የፊደልና የቁጥር መለያ (Alphanumeric Code) ይሰጣል።

ማጭበርበርን እና ወንጀልን የሚከላከሉ የደኅንነት ገጽታዎች
ይህ ዘመናዊ ሰሌዳ ከተሽከርካሪ ጋር ተያይዘው የሚፈጸሙ ወንጀሎችን፣ ስርቆቶችን እና ተመሳሳይ (የተደራረቡ) ታርጋዎችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት ታስቦ የተሰራ ነው። ሰሌዳው ፎርጀሪን (ማጭበርበርን) ለመከላከል የሚያስችሉ የሚከተሉትን የደኅንነት ባህሪያት አካቷል፦

የሆሎግራም እና የውሃ ምልክት (Watermark) * ማይክሮ ጽሑፎች (Microprinting)

በተለያዩ የብርሃን ሁኔታዎች (በሌሊትም ጭምር) በግልጽ እንዲታይ የሚያደርግ አንጸባራቂ ምልክት።

በተጨማሪም ሰሌዳው ለህዝብ እና ለህግ አስከባሪዎች በተለየ መልኩ የሚነበብ ስልታዊ የፊደላት አቀማመጥ የተከተለ ነው።

የዲጂታል ቴክኖሎጂ ትስስር እና ዘላቂነት
አዲሱ ሥርዓት ተሽከርካሪዎችን በቀላሉ ለመከታተል እና አስተማማኝ የዲጂታል መዝገብ ለመያዝ የሚያስችሉ እንደ ባርኮድ (Barcode)፣ ኪው አር ኮድ (QR Code) ወይም የአር ኤፍ አይ ዲ (RFID) ቺፖችን ይጠቀማል።

ከዚህም በላይ ሰሌዳዎቹ ለከባድ የአየር ሁኔታ መቋቋም ከሚችሉ ዘላቂ ቁሶች የተሰሩ በመሆናቸው እና ጥራታቸውን ጠብቀው ወጪ የሚቆጥቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጠቀሜታ አላቸው።

"አንድ ተሽከርካሪ — አንድ ሰሌዳ"
እንደ ሚኒስቴሩ መረጃ ከሆነ፣ አንድ ተሽከርካሪ ከተመዘገበበት ጊዜ ጀምሮ ከአገልግሎት ውጪ ሆኖ እስከሚወገድ ድረስ የሚገለገለው በአንድ ቋሚ ሰሌዳ እና በፊቱ መስታወት (Windshield) ላይ በሚለጠፍ ልዩ ስቲከር ብቻ ይሆናል።

ይህ አዲስ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ለውጥ በሀገሪቱ የትራፊክ ቁጥጥር፣ የጸጥታ ጥበቃ እና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ ይጠበቃል።

የመንገድና ትራንስፖርት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ፡፡*****ገንዳ ውሃ (ሰኔ 09/2018 ዓ.ም)የምዕራብ ጎንደር ዞን መንገድ፣ ትራንስፖ...
16/06/2026

የመንገድና ትራንስፖርት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ፡፡
*****
ገንዳ ውሃ (ሰኔ 09/2018 ዓ.ም)
የምዕራብ ጎንደር ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የ11 ወራት የሥራ አፈፃፀሙን ከማኔጅመንት አባላት ጋር በሰፊው ገመገመ። መምሪያው በቀሪዎቹ የበጀት ዓመቱ ቀናት ትኩረት የሚሹ አቅጣጫዎችንም አስቀምጧል።

በተደረገው የግምገማ መድረክ ላይ ባለፉት 11 ወራት የተመዘገቡ ስኬቶች የተፈተሹ ሲሆን፥ በተለይም በሚከተሉት ዘርፎች ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸው ተገልጿል፡

በመሠረተ ልማት፡ የዞኑን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ያደረጉ የመንገድ ግንባታ፣ የጥገና እና የድልድይ ግንባታ ሥራዎች፣

በአገልግሎት አሰጣጥ፡ የትራንስፖርት አገልግሎት ማሻሻያ እና የመናኸሪያዎችን አሰራር ወደ ተሻለ ስታንዳርድ የማሳደግ ተግባራት፣

በቁጥጥር ሥርዓት፡ የትራፊክ ቁጥጥርን ማጠናከር እና ሕገ-ወጥ የዋጋ ታሪፍን የመከላከል ሥራዎች በስፋት ተከናውነዋል።

እነዚህ የተከናወኑ ተግባራት በዞኑ የሚገኘው ማህበረሰቡ ቀልጣፋ የመጓጓዣ አገልግሎት እንዲያገኝና የመሠረተ ልማት ተደራሽነት እንዲያድግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከታቸው ተጠቅሷል።

የግምገማ መድረኩን የመሩት የምዕራብ ጎንደር ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ ኃላፊ አቶ አባይነህ ወረታ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ባለፉት ወራት የተመዘገቡ መልካም ተሞክሮዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል። በአፈፃፀም ሂደት የታዩ ክፍተቶችን በቀሪዎቹ ቀናት ውስጥ በተጠናከረ ክትትልና ቁጥጥር ለማስተካከል በቁርጠኝነት መሠራት እንዳለበትም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

"የበጀት ዓመቱ ማጠቃለያ ቀናት እጅግ ወሳኝ የሥራ ጊዜያት በመሆናቸው፥ ሁሉም የሥራ ክፍሎች የተጣለባቸውን ኃላፊነት በተገቢው ደረጃ በመወጣት የዓመቱን ዕቅድ 100% ለማሳካት በትጋት መንቀሳቀስ አለባቸው።"
— አቶ አባይነህ ወረታ (የመምሪያው ኃላፊ)

በግምገማው ማጠቃለያ ላይ እንደተመላከተው፤ መምሪያው በቀጣይም የሕዝቡን የትራንስፖርት ተደራሽነት ለማሳደግ፣ የመሠረተ ልማት ሥራዎችን በጥራትና በወቅቱ ለማጠናቀቅ፣ እንዲሁም የሕዝብን እርካታ ሙሉ በሙሉ ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ አስታውቋል። ይህ ተግባር መምሪያው ለልማት ሥራዎችና ለሕዝብ አገልግሎት ያለውን ታማኝነት በተግባር ያሳየበት መሆኑ ተገልጿል።

🔊 የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የ11 ወራት ዕቅድ አፈጻጸሙን ገመገመ፡፡*******ሰኔ 09/2018 (ደብትሎ)፦ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ትራንስ...
16/06/2026

🔊 የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የ11 ወራት ዕቅድ አፈጻጸሙን ገመገመ፡፡
*******
ሰኔ 09/2018 (ደብትሎ)፦ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የ11 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን ከመምሪያው ማኔጅመንትና ጠቅላላ ባለሙያዎች ጋር በጋራ መገምገሙን አስታወቀ።

በተጠናቀቀው የ11 ወራት የሥራ እንቅስቃሴ ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ በዕቅድ አፈጻጸም ሂደት የታዩ ጠንካራ ጎኖች እና ያጋጠሙ ደካማ ጎኖችን በዝርዝር የመለየት ሥራ ተከናውኗል።

የመምሪያው አመራሮችና ባለሙያዎች በጋራ ባደረጉት በዚህ ጥልቅ ግምገማ ላይ፦

የሥራ አፈጻጸሙን ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዱ የርብርብ ዘርፎች ተለይተዋል፤

በቀሪው የበጀት ዓመት ጊዜ ውስጥ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ዋና ዋና ተግባራት ላይ ስምምነት ላይ ተደርሷል፤

ተግዳሮቶችን በመቅረፍ ተቋማዊ ግቡን ለማሳካት የሚያስችል የቀጣይ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ እንደተገለጸው፣ ይህ የግምገማ መድረክ የታዩ ክፍተቶችን በጋራ ጥረት በመሙላት በቀሪው አንድ ወር ውስጥ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድን በስኬት ለማጠናቀቅ ትልቅ መነቃቃትን የፈጠረ ነው።

ደብትሎ — የደብረ ብርሃን ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የኮሚኒኬሽን ክፍል

የሁሉሰላም-ጎሽሜዳ መንገድ ሥራ ፕሮጀክትን በበጀት ዓመቱ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡******ባሕር ዳርበአማራ ክልል ሰሜን ጎጃም ዞን ደቡብ ሜጫ ወረዳ የሚገኘውና የአካባቢውን ማኅበ...
15/06/2026

የሁሉሰላም-ጎሽሜዳ መንገድ ሥራ ፕሮጀክትን በበጀት ዓመቱ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡
******
ባሕር ዳር
በአማራ ክልል ሰሜን ጎጃም ዞን ደቡብ ሜጫ ወረዳ የሚገኘውና የአካባቢውን ማኅበረሰብ የትራንስፖርት ችግር ያቃልላል ተብሎ የሚጠበቀው የሁሉሰላም-ጎሽሜዳ መንገድ ሥራ ፕሮጀክትን በተያዘው በጀት ዓመት ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ አስታወቀ።

ርዝመቱ 25.5 ኪሎ ሜትር የሆነውና በ2010 ዓ.ም የተጀመረው ይህ የገጠር መንገድ ፕሮጀክት፣ ኤጀንሲው በበጀት ዓመቱ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ካቀዳቸው ስትራቴጂካዊ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው።

የፕሮጀክቱን መጠናቀቅ የሚያፋጥኑ እና ከ3 እስከ 21.4 ሜትር ርዝመት ያላቸው 14 አነስተኛና መካከለኛ ድልድዮችን የመገንባት ሥራ በልዩ ትኩረት እየተከናወነ እንደሚገኝ ከኤጀንሲው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

እስከ ግንቦት መጨረሻ 2018 ዓ.ም ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎች፡

8 አነስተኛ እና መካከለኛ ድልድዮች ግንባታቸው ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል።

5 አነስተኛ ድልድዮች ከ65% እስከ 97% የሚደርስ ከፍተኛ አፈጻጸም ላይ ይገኛሉ።

የቀሪው 1 አነስተኛ ድልድይ ግንባታም 30% ደረጃ ላይ ደርሷል።

በአሁኑ ወቅት ያጋጠመው የነዳጅ እጥረት በፕሮጀክቱ የእለት ተእለት እንቅስቃሴ ላይ የራሱን አሉታዊ ጫና እያሳደረ ቢሆንም፣ የኤጀንሲው የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ችግሩን በጽናት በመቋቋም የተረፉትን ግንባታዎች በቀሪው ጊዜ አጠናቆ ፕሮጀክቱን ለማስረከብ በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየሰሩ ይገኛሉ።

ይህ መንገድ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ሲበቃ በአካባቢው ያለውን የግብርና ምርት ወደ ገበያ ለማውጣትና የሕዝቡን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለማጠናከር ትልቅ ሚና ይጫወታል።
ምንጭ ፦አማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ

የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የ11 ወራት ዕቅድ አፈፃፀሙን ገመገመ፡፡📅 ሰኔ 08/2018 ዓ.ም | ከሚሴየኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስ...
15/06/2026

የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የ11 ወራት ዕቅድ አፈፃፀሙን ገመገመ፡፡

📅 ሰኔ 08/2018 ዓ.ም | ከሚሴ

የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የ11 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ከመምሪያው ማኔጅመንት እና ጠቅላላ ባለሙያዎች ጋር በጋራ በመገምገም ላይ ይገኛል።

📌 በመድረኩ ላይ የተገኙ ቁልፍ የሥራ ኃላፊዎች፡

አቶ መሐመድ ሲራጅ ሙስጠፋ – የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ ኃላፊ

ኮማንደር ሁሴን እብራሒም – የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የወንጀል መከላከል ም/መምሪያ አዛዥ

የመምሪያው ሠራተኞች፣ የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ፖሊስ አመራሮችና አባላት።

📊 የውይይቱ ዋና ዋና ነጥቦች፡

የ11 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በአቶ ሠይፉ አስፋው የቀረበ ሲሆን፣ ባለፉት ወራት የተከናወኑ ተግባራት፣ የታዩ ጠንካራ ጎኖችና ያጋጠሙ ደካማ ጎኖች በዝርዝር ተገምግመዋል።

በበጀት ዓመቱ መከናወን ሲገባቸው በተፈለገው ደረጃ ያልተሳኩ ውስን ተግባራትን ለይቶ በማውጣት፣ በቀሪዎቹ ጥቂት ቀናት ውስጥ ሁሉም አካል ርብርብ በማድረግ ወደተሻለ አፈፃፀም እንዲያመጣቸው አቅጣጫ ተቀምጧል።

በአጠቃላይ መድረኩ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በሰፊው በመገምገም እና በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ዘርፎችን በመለየት የቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል።

📌 በባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ የአንዳሳ ቁጥር 1 ተንጠልጣይ ድልድይ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ ፡፡****በሰሜን ጎጃም ዞን በባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ ለረጅም ጊዜ የማህበረሰቡ ጥያቄ የነበረ...
15/06/2026

📌 በባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ የአንዳሳ ቁጥር 1 ተንጠልጣይ ድልድይ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ ፡፡
****
በሰሜን ጎጃም ዞን በባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ ለረጅም ጊዜ የማህበረሰቡ ጥያቄ የነበረው የአንዳሳ ቁጥር 1 ተንጠልጣይ ድልድይ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለተጠቃሚው ማህበረሰብ ተረከበ።

ይህ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የድልድይ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ፣ በአካባቢው ይስተዋል የነበረውን የወንዝ መሻገሪያ እና የትራንስፖርት ችግር በዘላቂነት እንደሚቀርፍ ተገልጿል።

🏗️ የባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት
የድልድዩ ግንባታ ጥራቱንና ደረጃውን ጠብቆ እንዲጠናቀቅ የበርካታ አካላት የላቀ ቅንጅትና ንቁ ተሳትፎ የታየበት እንደነበር ተጠቁሟል። በዚህም መሠረት፦

የግንባታ ስራው፦ በ"ዋልታ የገጠር መንገድ ሥራ ባለሙያዎች ህብረት ስራ ማህበር" ተቋራጭነት፤

የአማካሪነት ስራው፦ በ"3ኤኤች (3AH) ኢንጂነሪንግ" አማካሪነት፤ እንዲሁም

የክትትልና ድጋፍ ስራው፦ በሰሜን ጎጃም ዞን እና በባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ የዘርፉ ባለሙያዎች ንቁ ተሳትፎና እገዛ የተከናወነ ነው።

🎯 የፕሮጀክቱ ፋይዳና ማጠቃለያ
"ድልድዩ ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ሆኗል"

የአካባቢው ነዋሪዎች በተለይም በክረምት ወቅት ወንዙን ለመሻገር ይደርስባቸው የነበረውን እንግልት በማቃለል ረገድ ይህ ተንጠልጣይ ድልድይ ትልቅ ሚና ይጫወታል። ግንባታው ተጠናቆ ዛሬ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም ለአገልግሎት በይፋ በመረከቡ ማህበረሰቡ የተሰማውን ደስታ የገለጸ ሲሆን፣ መሰረተ ልማቱ የክልሉን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ፍሰት ይበልጥ ቀልጣፋ እንደሚያደርገው ታምኖበታል።

Address

Amhara
Bahir Dar
6000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara RoadTransport and Logistics Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Amhara RoadTransport and Logistics Bureau:

Share