Shalamw Abrar

Shalamw Abrar Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Shalamw Abrar, Grocers, Dire Dawa.

14/06/2026

በኃይል ፍላጎትን የማስፈጸም አካሄድ እስካልተለወጠ ድረስ በፖለቲካችን ዉስጥ ሐቀኛ ለዉጥ ለማምጣት አይቻልም፡፡ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚደረገዉ ጥረት ዋንኛዉ ደንቃራ በኃይል ስልጣንን ለማስጠበቅና ለመቆጣጠር የሚደረገዉ ጥረት ነዉ፡፡ ሥልጣን ሕጋዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ የሚገኝበትን መንገድ ካላጠናከርን በስተቀር፤ ፖለቲካችን ከአዙሪት ሊላቀቅ አይችልም፡፡

- የመደመር መንግሥት ገጽ 387

#መደመር #የመደመርመንግስት

13/06/2026

እንደ ወሎ ዕጣን

ደሴ ገብተናል። ቡና ለመጠጣት ከአንድ የጀበና ቡና ቤት ጎራ ብለናል። እስካሁን ከአዕምሮዬ ጓዳ ያልጠፋ፤ በምናቤ እየተመላለሰ የሚያውደኝ ልዩ የዕጣን ጢስ መዓዛ "እንኳን ደህና መጣችሁ" ብሎ ተቀብሎናል። በዕጣን ጢስ የታጀበ የቡና አቀራረብ የተለመደ ቢሆንም የወሎ ግን ይለያል። ዕጣን በየአይነቱ ይታያል። ማጨሻው ቆስቆስ ይደረግና ዕጣን ጣል ይደረግበታል። በጢሱ አንድ አይነት መልክ ይጋሩና ወደ ላይ ይምዘገዘጋሉ። ውድ ሽቶ የሚያስንቅ ግሩም መዓዛም ይመግባሉ። ስለዕጣኑ ተደንቀን ስናወራ እንግዳ መሆናችን የገባት ባለቡናዋ ልጅ ወደ ዕጣን ተራ ጠቆመችን።

በቀለምም በመዓዛም የተለያዩ የዕጣን አይነቶችን አየን። ደሴ ከተማ አራዳ ገበያ አካባቢ የመንገዱ ግራና ቀኝ በውብ ቀለማት አሸብርቆ በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አረንጓዴ ቢጫና ቀይ ቀለማት የተሰደሩ የወሎ ጢስ ግብአቶች ለደንበኛ ቀርበው ተመለከትን።

በዚህ ቅጽበት አንድ ግጥም ትዝ አለኝ። ገጣሚው ቆንጆዋን ሴት “ራያ ነሽ የጁ ባቲ ነሽ ከሚሴ፣ ጠረንሽ የሚለው አሽኩቲና ከሴ” እያለ ሲያወድስ በራያ፣ በየጁ፣ በባቲ እና ከሚሴ ከሚገኙት የወሎ ጢስ ጠረን እና ውብ መዓዛ ጋር ያመሳስላታል።

የወሎ ጭሳጭሶች ዝናቸው በኢትዮጵያ ምድር የናኙት፤ የፈረንሳይን ሽቶ የሚያስንቅ ልዩ ጠረን የተቀዳጁት ወይባ፣ ቡክቡካ፣ ቅጥቅጥ፣ ስምቡል፣ ቆቦ ጭስ፣ ደውሌ፣ ሶርሳ፣ አርቲ፣ አሽኩቲ፣ ጠጅ ሳር፣ አደስ፣ ሚጢ፣ ከርቤ፣ ድኝ፣ ወገርትና ቀበርቾ ተደምረው በፈጠሩት ልዩነት ነው።

አንድ የእጣን አይነት በመልኩም በመዓዛውም የተለየ ትኩረት አይስብም ይሆናል። ነገር ግን አንዱ ከሌላው ጋር ሲሆን አይን ውስጥ ይገባል። ተፈላጊነቱም ይጨምራል። የዕጣን አይነቶቹ ለመዲሃኒትም የሚያገለግሉ በመሆናቸው ተፈላጊነታቸው ይጨምራል።

እኛ ኢትዮጵያዊያን ላንለያይ የተጋመድን፤ ላንነጣጠል የተዋሃድን ህዝቦች ነን። እንደ ዕጣን ጢስ አይነቶች በአይነትና በመልክ ብንለያይም፤ በልዩነት ውስ የምንደምቅ ህዝቦች ነን። ብሄር ብሄረሰቦች የኢትዮጵያ ልዩ ፀጋዎች ናቸው። እያንዳንዱ ብሄር ብሄረሰብ ያለው ባህል፣ እሴት፣ ቋንቋ፣ ታሪክ የብዝሃነት ሀብቶች ናቸው። እነዚህ ብዝሃ ሀብቶች ከጌጥነት አልፎ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ ፋይዳቸው የላቀ ነው። በአንድነት ቆመን አቅሞቻችንን ስንሰበሰብ ከማጌጥም በላይ ሁለንተናዊ አቅማችንም የጎለበተ ይሆናል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) ከመደመር ዕሴቶች መካከል አንዱ አገራዊ አንድነት መሆኑን በመደመር መጽሐፍ ላይም ጽፈዋል። በመጽሐፉ ገፃ 47 ላይ እንደተብራራው ሀገራዊ አንድነት ማንነታችን እንዳንለያይ ሆኖ የተጋመደ፣ የተሰናሰለ የተዋሃደ መሆኑን አመላካች ነው። የሀገራችን ብሄሮች እጣ ፋንታ በጋራ ለማደግ የተሰራ ብቻ እንጂ ተለያይተን ወይም ተነጣጥለን ሉዓላዊ ሀገር ሆነን፤ የነጠላ ማንነታችንን አስጠብቀን በሰላም መቆየት አንችልም። ሀገራዊ አንድነታችን የምርጫ ብቻ ሳይሆን የህልውና ማስጠበቅ ጉዳይ ጭምር ነው።

ስንደመር በህብረትም ስንቆም እንደወሎ እጣን በመልክ እናጌጣለን። በመዓዛችንም ዓለምን እናስቀናለን። የከበረች፤ በሁለንተናዊ ዕድገትም ተምሳሌት የሆነችው ኢትዮጵያን እንገነባለን።

13/06/2026
13/06/2026

“የመደመር መንግሥት ታሪክን ከማውራት ይልቅ ታሪክን በመሥራት ራሱን መግለጥ የሚሻ ነው፤ የሚያሻግር ሐሳብ፣ የሚሻገር ትውልድ ይዞ ለለውጥ የሚተጋ፣ ራሱን እንደ ሻማ አቅልጦ ትውልድ የሚያሻግር ሥርዓት ነው።” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

13/06/2026

በሀገራችን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመገንባትና በሐሳብ ላይ የተመሰረተ ፖለቲካን ለማዳበር ዋነኛዉ ፈተና ያልተለወጠ የትግል ስልትና ያልዳበረ የፖለቲካ ባህል ነዉ፡፡

የዴሞክራሲ ምህዳርን በማስፋት የተለያዩ ሐሳቦች እንዲደመጡ፤ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን በማድረግ ሥልጣን በሕዝብ ድምጽ ብቻ እንዲገኝ ለማድረግ የተደረገዉ ጥረት፤ በብዙ ፈተናዎች ዉስጥ ያለፈ ነዉ፡፡

በሀገራችን ያለዉ ፖለቲካዊ እዉነታ ሐሳብ እንዲያሸንፍ ሳይሆን ኃይል እንዲያሸንፍ የሚያስችል ነዉ፡፡

ይህ ከነባር ባህልና ከፖለቲካ ባህል ይመነጫል፡፡ በነባሩ ባሕል ገዳይ አሸናፊ ነዉ፡፡ ገዳይ ጀግና ነዉ፡፡

የተሻለ የዉይይትና የክርክር ባህል የነበራቸዉ ማኅበረሰቦች እንኳን ይሄንን ባህል ማስጠበቅ አልቻሉም፡፡ - የመደመር መንግስት ገጽ - 386

#መደመር
#የመደመርመንግስት
#የሐሳብየበላይነት
#ዴሞክራሲ

12/06/2026

Address

Dire Dawa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Shalamw Abrar posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category