Ethiopian Drama

Ethiopian Drama Ethiopian Drama, Movies, Music, Comedy and everything Ethiopian.

የቴዲ አፍሮ የቀድሞው ማናጀር አቶ አዲስ ገሰሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። የጃኖ ባንድ መስራች የነበሩት እና የሙዚቀኛ ዘለቀ ገሰሰ ወንድም የሆኑት ታዋቂው የሙዚቃ ፕሮዲዮሰርና ማኔጀር አቶ አ...
19/06/2026

የቴዲ አፍሮ የቀድሞው ማናጀር አቶ አዲስ ገሰሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

የጃኖ ባንድ መስራች የነበሩት እና የሙዚቀኛ ዘለቀ ገሰሰ ወንድም የሆኑት ታዋቂው የሙዚቃ ፕሮዲዮሰርና ማኔጀር አቶ አዲስ ገሰሰ በአሜሪካን ሀገር ህይወታቸው ማለፉን የቅርብ ወዳጆቻቸው ለመዝናኛ ሚዲያ አስታወቁ።

አቶ አዲስ ዓለም አቀፍ ዝና ያተረፉትን የቦብ ማርሊ ልጆችንእና በርከት ያሉ ታዋቂ ሙዚቀኞችን የማማከርና የማስተዳደር ስራ የሰሩ ጉምቱ የሙዚቃ አስተዳደር ባለሞያ ነበሩ። አቶ አዲስ የቴዲ አፍሮ ማኔጀር በመሆንም ለረጅም ጊዜ አገልግለዋል።

በትላንትናው እለት አመሻሹ ላይ በኒው ጀርሲ ግዛት ህይወታቸው ያለፈው አቶ አዲስ ገሰሰ ፣ የሞታቸው ምክንያት ለጊዜው ያልታወቀ ሲሆን አስከሬናቸውን ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ እንደታሰበ የደረሰን መረጃ ያመለከታል።

@መዝናኛ ሚዲያ

የድሮ ወዳጅነት እና የዛሬው ዝምታ፦ ለ"ዋሸው እንዴ" አዘጋጆች 👉 የይቅርታ ጊዜው አሁን ነው! ኮሜዲያን ታሪኩ ✍️  *ከሰሞኑ ኮሜዲያን አሌክስ በጠና ታሞ አልጋ ላይ መዋሉን በማህበራዊ ሚዲያ...
18/06/2026

የድሮ ወዳጅነት እና የዛሬው ዝምታ፦ ለ"ዋሸው እንዴ" አዘጋጆች 👉 የይቅርታ ጊዜው አሁን ነው! ኮሜዲያን ታሪኩ ✍️

*ከሰሞኑ ኮሜዲያን አሌክስ በጠና ታሞ አልጋ ላይ መዋሉን በማህበራዊ ሚዲያ ስመለከት በእጅጉ አዝኛለሁ። አሌክሶ፣ ፈጣሪ ጤናህን ይመልስልህ፤ ጨርሶ ይማርህ!

በዚህ አጋጣሚ የግል ትዝብቴን ላጋራችሁ እወዳለሁ። "ዋሸው እንዴ" የመዝናኛ ፕሮግራም በአባይ ቲቪ ሲጀመር፣ ከመስራቾቹ አንዱ የነበረው አሌክስ ከወዳጆቹ ጋር የነበረው ትስስር በጣም ጠንካራ ነበር። በስራ ብቻ ሳይሆን በወንድማማችነት ረጅም ጊዜን አብረው አሳልፈዋል።

የምንጊዜም ባልንጀሮች የነበሩት እነዚህ የፕሮግራም አዘጋጆች፣ ለመኝታ ካልሆነ በቀር ውሎና ምሽታቸውን "በያ" እየተባባሉ እስኪጠራሩ ድረስ የጠበቀ ወዳጅነት ነበራቸው። ነገር ግን ከእለታት በአንድ ቀን፣ አለመግባባት ተፈጥሮ "እቃቃ ፈረሰ ዳቦ ተቆረሰ" ሆኖ ነገሩ ተበላሸ። አሌክስ ከፕሮግራሙ ተለየ፤ ከዚያም ወዲያ መራራቁ ተፈጠረ።

የሚገርመውና የሚያሳዝነው ጉዳይ ግን ይህ ነው። ሌላው ኮሜዲያን (ፍልፍሉ) በታመመ ጊዜ፣ እነዚህ የፕሮግራም አዘጋጆች "እኔ ልታመምልህ" በሚያስብል ደረጃ በሁሉም አቅጣጫ ተረባርበው አብረውት ነበሩ። ታዲያ ዛሬ አሌክስ በጠና ሲታመም፣ ያ የድሮ የቅርብ ወዳጅነታቸው ወዴት ሄዶ ነው "እግዜር ይማርህ" ለማለት እንኳን የተሳናቸው?

ለታይታ አበባ ጉንጉን ከመሮጥ፣ በችግር ጊዜ ደጉን ዘመን አስታውሶ መጠየቅ ይበልጥ የሰውነት መገለጫ ነው። እንደ ድንበር በቅንድብ መተያየቱን ትታችሁ፣ በይቅር ባይነት ልባችሁን ለምን አልከፈታችሁም?

ለዚህም ነው የምለው፦
ዛሬም አረፈደምና ልባችሁን ለይቅርታ ክፈቱ። የትላንቱን መልካም ጊዜ አስታውሱና ከጎኑ በመሆን ጠላትን ኩምሽሽ፣ ሰይጣንን ሀፍረት አከናንቡት!

@ኮሜዲያን ታሪኩ ሰማኒያ — ከአሜሪካ

መንሱር በእስር ቤት ተረሳ! ዛሬ የፍ/ቤት ቀጠሮ ነበር።የ"ፊንቴክ" የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡየ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንትን ሽፋን በማድረግ በተፈጸመ መጠነ-ሰፊ የማጭበር...
18/06/2026

መንሱር በእስር ቤት ተረሳ! ዛሬ የፍ/ቤት ቀጠሮ ነበር።

የ"ፊንቴክ" የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ

የ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንትን ሽፋን በማድረግ በተፈጸመ መጠነ-ሰፊ የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ ታዋቂ አርቲስቶች እና የቲክቶክ አንቂዎች ዛሬ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ፊት ቀርበዋል።

በእስር ላይ የሚገኘውን 5ኛ ተከሳሽ መንሱር ጀማልን ጨምሮ፣ በዋስትና መብት በውጭ ሆነው ጉዳያቸውን የሚከታተሉት ቀሪዎቹ ተጠርጣሪዎች በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት ቀርበው በጠበቆቻቸው አማካኝነት የክስ መቃወሚያ አቅርበዋል።

የ1ኛ ተከሳሽ ጠበቆች የ5 ገፅ፣ እንዲሁም የሌሎቹ ተከሳሾች ጠበቆች እያንዳንዳቸው ባለ 6 ገፅ የክስ መቃወሚያ ለችሎቱ ያስገቡ ቢሆንም፣ የቀረበለትን ሰፊ የክስ መቃወሚያ በዛሬው ዕለት ተመልክቶ ምላሽ መስጠት እንደማይችል አቃቤ ህግ ለችሎቱ አስታውቋል።

ፍርድ ቤቱ የአቃቤ ህግን ጥያቄ በመቀበል፣ የቀረቡትን የክስ መቃወሚያዎች መርምሮ ምላሽ ለመስጠት ለሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ዘገባው የሸገር ኤፍ ኤም ነው።

ላለፉት ሶስት አመታት በኢቢኤስ ቴሌቪዠን ሲታይ ቆይት ሚያዚያ 4 ቀን 2018 ዓ ም ወደ ቻናል ዋን ቲቪ ተዘዋውሮ ሲታይ የነበረው  " በስንቱ " የተሰኘው የቴሌቪዠን ድርማ  መታገዱ ተሰማ ።...
17/06/2026

ላለፉት ሶስት አመታት በኢቢኤስ ቴሌቪዠን ሲታይ ቆይት ሚያዚያ 4 ቀን 2018 ዓ ም ወደ ቻናል ዋን ቲቪ ተዘዋውሮ ሲታይ የነበረው " በስንቱ " የተሰኘው የቴሌቪዠን ድርማ መታገዱ ተሰማ ።

በስንቱ ድራማ ለዕገዳ ያበቃው ምክንያት የድራማው ፕሮዲውሰር የሆነው " አብሪኮም መሌቲሚድያ " ከኢቢኤስ ቴሊቪዠን ጋር በገባው አለመግባባት መህኑ ታውቋል ።

ኢቢኤስ ቲቪ የድራማው ባለመብት ቀመሆኔ ከኔ ይሁንታ እና እውቅና ውጪ ድራማው ወደ ሌላ ቲቪ ተጣቢያ ሄዳል ይህ ደግም አግባብ ባለመሆኑ ድራማው ይታገድልኝ የሚል ጭቤጥ ያለው ክስ በማቅረቡ እንደሆነ አውቀናል ።

አብሪኮም መልቲሚዴያ በበኩሉ ከኢቢኤስ ቲቪ ጋር የነበረኝን ኮንትራት በመጨረሴ ነው ወደሌላ ተቋም ያመራሁት የሚሌ መከራከሪያ አቅርቦ የነበረ ቢህንም ጉዳዩን ሲመለከት የነበረው የፌደራሌ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ብሌምድብ አራተኛ ፍታብሄር ችሎት የድራማው እግድ ጥያቄን እንደተቀበለ አውቀናል ።

በዚህ የፍርድ ቤት ውሳኔ መሰረት ዘወትር ረቡዕ በቻናል ዋን ቲቪ ላይ ይታይ የነበረው በስንቱ ድራማ መቆሙ ታውቋል ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በበስንቱ ድራማ ላይ የሚሰሩት ተዋንያን ድራማው በኢቢኤስ ቲቪ እየታየ በነበረበት በቅት ድራማውን የሰሩበት ክፍያ እንዳልተከፈላቸው ገለፁ ።

ከመሪ ተዋንያን እስከረዳት ተዋንያን ያሉ የበስንቱ ድራማ አርቲስቶች ድራማው በኢቢኤስ ቲቪ ሲተላለፍ የነበረ የሁለት የሁለት ክፍል ክፍያ እንዳልተሰጣቸው ለዝግጅት ክፍላችን ገልፀውልናል ።

ስማችን አይጠቀስ ያሉ እነዚሁ የበስንቱ ድራማ ተዋንያን የሰራንበት ክፍያ እንዲሰጠን በተደጋጋሚ ፕሮዲውሰሩን ብንጠይቅም ሊፈፀምልን ሳየችል ቀርቷል አሁን በአዲሱ የቲቪ ቻናልም የተላለፈው የድራማው ክፍያ ሊፈፀምን አልቻለም ሲሉ ቅሬታቸውን ለዘ-ሐበሻ ገልፀዋል ።

በዚህ ቅሬታ ላን አስተናየታቸዌን እንዲሰጡን የአብሪኮም ሃላፊዎች ጋር ብንደውልም ስልካቸው ስለማይነሳ ምላሽ ማግኘት ሳንችል ቀርተናል የዝግጅት ክፍላችን የበስንቱን ፕሮዲውሰሮች ምላሽ ካላቸው ለማስተናገድ ዝግጁ እንደሆንን ለመግለፅ እንወዳለን ።

@ዘ-ሐበሻ መዝናኛ ዜና

15/06/2026

የአንጋፋው ድምፃዊ ሰማኽኝ በለው ድንገተኛ ማረፍን ተከትሎ ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገለጸ።

ቴዲ አፍሮ ይፋ ባደረገው ይፋዊ የሐዘን መግለጫ መልዕክት፣ በአንጋፋው አርቲስት ድንገተኛ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማውን ከፍተኛ ሐዘን በመግለጽ፣ ለሟች ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶች እንዲሁም ለመላው የሙያ አድናቂዎች ከልብ የመነጨ መጽናናትን ተመኝቷል።

መልእክቱ
" በተወዳጁ ና በአንጋፋው ድምፃዊ ስማኽኝ በለው ድንገተኛ ሕልፈት ሕይወት የተሰማኝን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽኩ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለሙያ አድናቂዎቹ በሙሉ ከልብ መጽናናትን እመኛለው::

ነፍስ ይማር!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር
ፍቅር ያሸንፋል
ቴዎድርስ ካሳሁን
(ቴዲ አፍሮ)

ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የ...
15/06/2026

ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡

ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያዩ ባህላዊ እና ሌሎች ይዘቶቸ ያሏቸው የሙዚቃ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አበርክቷል፡፡

ድምጻዊው ለሕዝብ ካበረከታቸው የሙዚቃ ሥራዎች መካከል ነይ ዘመድዬ፣ እንዴት ነሽ፣ ደቦት እንስራ፣ ዘና በይ፣ ባላገር እና ሌሎች ይገኙበታል፡፡

ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት እንደነበር ፋና ዲጂታል ከቤተሰቦቹ ያገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

Ethiopian Drama ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለአድናቂዎቹ መጽናናትን ይመኛል፡፡

Via FBC

ሦስት አገሮች በጋራ ያዘጋጁት የዓለም ዋንጫ  : ከዘጠኝ አሠርታት በላይ ያስቆጠረው የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ዘንድሮ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ሦስት አገሮች ሜክሲኮ፣ ካናዳና አሜሪካ በጋራ ያዘ...
11/06/2026

ሦስት አገሮች በጋራ ያዘጋጁት የዓለም ዋንጫ

: ከዘጠኝ አሠርታት በላይ ያስቆጠረው የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ዘንድሮ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ሦስት አገሮች ሜክሲኮ፣ ካናዳና አሜሪካ በጋራ ያዘጋጁታል፡፡
ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማኅበር እንዳስታወቀው፣ የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ነገ ሐሙስ ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. በሜክሲኮ ሲቲ በሚኖረው ታሪካዊ የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት የሚጀምር ሲሆን፣ በማግስቱም በቶሮንቶና ሎስ አንጀለስ እንዲሁ በጥበባዊ ድግስ ይጀመራል፡፡
አሜሪካ እ.ኤ.አ. በ1994፣ ሜክሲኮ ደግሞ በ1970 እና 1986 ውድድሩን ያስተናገዱ ቢሆንም፣ ካናዳ ግን ውድድሩን ስታስተናግድ ይህ የመጀመሪያዋ ይሆናል።

Ethiopian reporter

ከተወዳጁ ባለቤቴ ጎን ቅበሩኝ ብለው እንደተናገሩ አረፉ  የታዋቂው አርቲስትና ተባባሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ገሠሠ የረጅም ዘመን የትዳር አጋር የነበሩት ወይዘሮ መንበረ ግርማ በ75 ዓመታቸው ከዚህ...
07/06/2026

ከተወዳጁ ባለቤቴ ጎን ቅበሩኝ ብለው እንደተናገሩ አረፉ

የታዋቂው አርቲስትና ተባባሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ገሠሠ የረጅም ዘመን የትዳር አጋር የነበሩት ወይዘሮ መንበረ ግርማ በ75 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ለ37 ዓመታት ያህል በትዳር አብረው የዘለቁት ወይዘሮ መንበረ ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ማረፋቸው ታውቋል።
የስንብት እና የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ሰኞ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ በ9 ሰዓት በቅድስት ሥላሴ መንበረ ፅባህ ካቴድራል ይፈጸማል።
ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለናፈቋቸው ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን።

ኮሜዲያን አሌክስ ፈጣሪ ይማርህ !በስታንዳፕ ኮሜዲ ስራዎቹ በርካታ ስራዎችን ያበረከተልን ፣ ዋሸው እንዴ የተሰኘው ፕሮግራም ከመስራቾቹ አንዱና አቅራቢ ፣ አርትስ ቲቪ ላይ የ90ዎቹን ፕሮግራም...
06/06/2026

ኮሜዲያን አሌክስ ፈጣሪ ይማርህ !

በስታንዳፕ ኮሜዲ ስራዎቹ በርካታ ስራዎችን ያበረከተልን ፣ ዋሸው እንዴ የተሰኘው ፕሮግራም ከመስራቾቹ አንዱና አቅራቢ ፣ አርትስ ቲቪ ላይ የ90ዎቹን ፕሮግራምን የመራ ፣ በቅርቡም ኢቢኤስ ቲቪ ላይ የቤተሰብ ጨዋታን ለመምራት
የተወዳደረና ብቃቱን ያሳየን ፦

ጨዋታ አዋቂው ፣ ጥርስ የማያስከድነው
እጅግ ሰው አክባሪው ኮሜዲያን አሌክስ በጠና ታሞራስ ደስታ ሆስፒታል ድንገተኛ ክፍል ይገኛል።

ፈጣሪ ለቤተሰቦቹ ፣ ለሚወዳቸው ልጆቹ ሲል ምህረቱን ይላክለት።
ቤተሰቦቹ ፣ ወዳጅ አድናቂዎቹ በፀሎታችሁ አስቡት !
አሌክስ አይዞን የምታምነው ፈጣሪ ይምርሃል።
አክባሪና አድናቂ ወንድምህ
ዘሪሁን ተዝናኑ !!!

Address

London

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Drama posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share