08/09/2026
የቁንጅና አምባሳደራችን ሩት አዲስ አበባ ገብታለች!
በ75ኛው የዓለም ቁንጅና ውድድር (Miss World) ላይ ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ በኩራት ወክላ የተመለሰችው ውዷ እህታችን ሩት፣ ወደ እናት ሀገሯ ስትመለስ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት የክብር አቀባበል ተደርጎላታል።
በአቀባበል ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የብዙዎችን ቀልብ የሳበውና የብዙዎችን አንጀት የበላው አፍታ—የሩትና የአባቷ ስሜት ቀስቃሽ መገናኘት ነበር። በዓለም መድረክ ያሳየችውን ፅናትና ያመጣችውን ክብር ያዩት አባቷ፣ ልጃቸውን በሞቅታ አቅፈው ለረጅም ደቂቃዎች ፍቅራቸውን ሲገልጹ ይታዩ ነበር።
ሀዘኗን ወደ ብርታት ቀይራ፣ ባህሏንና ማንነቷን የሚያንጸባርቅ ባህላዊ አልባሳት አጊጣ ሀገሯን ስታስጠራ የቆየችው ሩት፤ ከአባቷና ከወዳጅ ዘመዶቿ ጋር ያሳየችው ይህ የስሜት ውህደት ኢትዮጵያዊ የቤተሰብ ፍቅርንና ጥንካሬን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አስመስክሯል።
ሩት—ይህ አቀባበል ላሳየሽው የማይወላወል ጥረትና ለሀገርሽ ላስገኘሽው ክብር የሚገባሽ ጥቂት ስጦታ ነው።
እንኳን ወደ እናት ሀገርሽ በሰላም ተመለስሽ!
🇪🇹🙏
ጉርሻ page