06/22/2026
አዲስ አበባ በቃላት ብቻ ሳይሆን በተጨባጭ ተግባር፤ የህዝብን አመኔታ በክብር ለመመለስ ጉዞ ላይ ናት
እውነተኛ መሪነት የህዝብን ድምፅ በጥልቅ ምስጋና ተቀብሎ፣ ወዲያውኑ ወደ ታላቅ የልማት አሻራ መቀየር ነው። የኢትዮጵያ የብልፅግና መንገድን ዳግም ለመምራት የ5 ዓመት ሙሉ እምነት በተሰጠን በማግስቱ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ታሪክ የሚዘክረው፣ የሰውን ልጅ ክብር ከፍ የሚያደርግ ታላቅ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ንቅናቄን በይፋ አስጀምሯል።
ከከንቲባ ጽሕፈት ቤት ጀርባ የነበረውን እጅግ የተጎሳቆለና ለኑሮ ምቹ ያልሆነ ሰፈር ወደ ዘመናዊ፣ ውብና ንጹህ መንደር ለመቀየር ግዙፉ የ“አራዳ የበጎነት መንደር” ግንባታ ዛሬ ተጀምሯል። ይህ ተራ የመኖሪያ መንደር አይደለም፤ የከተማችንን ገጽታ ሙሉ በሙሉ የሚቀይርና የነዋሪዎቿን የኑሮ ደረጃ የሚያዘምን ታላቅ ፕሮጀክት ነው።
ለከተማዋ ነዋሪዎች ምቹና ክብር የሚመጥን ዘመናዊ አኗኗርን ለመፍጠር፣ ሌት ተቀን ለምትተጉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሪዎችና በጎ ፈቃደኞች በሙሉ—ምስጋናና አክብሮት ለእናንተ ይሁን! ህዝብ የሰጠውን አደራ በተግባር እየመለሳችሁ ነውና ታሪክ ሁልጊዜም ሲያወድሳችሁ ይኖራል።
ከተማችን ውብ፣ ለኑሮ ምቹና የነዋሪዎቿ ክብር የሚጠበቅባት እስክትሆን ድረስ ስራችን በቁርጠኝነት ይቀጥላል!